Saturday, April 13, 2013


በጣም አጭር ወሬ፤ “ፍትህ ናፈቀን!”

541466_10151574603824743_1208444829_n
Legg til bildetekst
ዛሬም ኢትዮጵያውያን ሙስሊሞች የፍትህ ናፍቆት እንዳንገላታቸው ጮክ ብለው ለመንግስት ተናግረዋል፡፡ መንግስት መስማት እና አለመስማቱን ለማጣራት ያደረኩት ሙከራ የለም፡፡
ምክንያቱም መንግስታችን የጆሮ ህክምና ላለማድረግ ቆርጦ ስለተነሳ፤  ከዚህም በበለጠ በርከት ብለን አብረን እና ተባብረን ካልጮህንለት በስተቀር እንደማይሰማን ስለጠረጠርኩ መሆኑ ይታወቅ፡፡
በዛሬው የሙስሊም ኢትዮጵያውን ተቃውሞ በይበልጥ ጎልቶ የወጣው “ፍትህ ናፈቀን” የሚል ቃል ሲሆን ነገሩን በጭምጭምታ የሰሙ የመንግስት ቤተዘመዶች “ፍትህ ፍትህ… ፍትህ ምን ነበር…?” ብለው ሲጠይቁ ተሰምቷል፡፡

One Response to በጣም አጭር ወሬ፤ “ፍትህ ናፈቀን!”

No comments:

Post a Comment