ፍየል ወዲህ…” – ይኸነው አንተሁነኝ
ሚያዚያ 23 2013
“ከእንግዲህ የገበሬው ችግር የርሃብ ችግር ሳይሆን የሚያመርተውን የተትረፈረፈ ምርት በርካሽ እንዳይጥለውና በገንዘብ መልክ የሚኖረው ገቢ እንዳያንስበት ነው፡፡” ባለራዕዩ መለስ ዜናዊ በዘመነ አካለ ስጋው የወሸከተው ደርዝ የሳተ ቃል
“ከእንግዲህ የገበሬው ችግር የርሃብ ችግር ሳይሆን የሚያመርተውን የተትረፈረፈ ምርት በርካሽ እንዳይጥለውና በገንዘብ መልክ የሚኖረው ገቢ እንዳያንስበት ነው፡፡” ባለራዕዩ መለስ ዜናዊ በዘመነ አካለ ስጋው የወሸከተው ደርዝ የሳተ ቃል
የተለያዩ መንግስታት ሕዝባቸውን ለማስተዳደርና ቁሳዊ መንፈሳዊና ኢኮኖሚያዊ ፍላጎታቸውን ለማሟላት፣ የሀገራቸውን ጸጥታና ደህንነት አስጠብቆ ለመምራት፣ እንዲሁም ከሌላው ዓለም ጋር ጥቅምን ያገናዘበ ግንኙነት ለመመስረት የሚያግዙ የተለያዩ ፖሊሲዎችን ያጸድቃሉ ይተገብራሉም። አፈጻጸሙንም በተመለከተ የተለያዩ መመዘኛዎችን በማውጣት ይከታተላሉ፤ ተጠቃሚውን ምሕበረሰብ መሰረት ያደረገ የእርምት እርምጃዎችንም መውሰድ ከአንድ መንግስት ነኝ ከሚል አካል የሚጠበቅ ሃቅ ነው። ይህ ሲሆን እንግዲህ የተዘጋጁትን ፖሊሲዎች፣ አተገባበራቸውንና ሊያመጡ የሚችሉትን ውጤት በተመለከተ የሚወጡ መንግስታዊ ቅድሚያ መግለጫዎችም ሆኑ ማብራሪያዎች ከዚያም ሲያልፍ እቅዶችና የተስፋ ቃሎች በሙሉ በባለሙያ የተቃኙና በመሰረታዊ የትንበያ ሳይንስ የተዳሰሱ ሊሆኑ መቻላቸው አያጠያይቅም እጅግ በጣም ቢያንስ ሃላፊነትና ተጠያቂነት ለሚሰማቸው መንግስታት። ፍየል ወዲህ…
No comments:
Post a Comment