*ከ95% የማያንሰው vs 5% የማይሞላ***
ጋዜጠኝነት ለኢትዮጵያ ኢትዮጵያም ለጋዜጠኝነት የማትመች አገር መስላለች፡፡
1 ብእርን የጨበጡ፣ በሀሳባቸው ብልጫ ውድድሩን ለማሸነፍ የጣሩ፣ ሀሳባቸውን በጽሁፍ ሆነ በንግገር መግለጣቸው እንደነውር ተቆጥሮ ዶክመንተሪ የሚሰራባት፡፡ ሰብዓዊ መብት፣ፍትህ፣እኩልነት እነደማዕድን ተቆፍሮ እንኳን የማይገኝባት ሀገር ሆናለች ኢትዮጵያ፡፡
2 ዲሞክራሲ እንደ ሰማይ የራቃት፣ ችጋር ስጋዋን አልፎ አጥንቷን መብላት የጀመረባት፤ ለለውጥ የተነሱ አብረን ተባብረን ወደ ፊት እንራመድ ያሉ እንደ አረም እየተመነጠሩ የሚታሰሩባት ሀገረ መከራ ሆናለች ኢትዮጵያ፡፡
3 አንድነቷ ተጎንጉኖ የዘር እራቁትነት የለበሰች፣ ነገ እርስ በእርስ እንዳንበላላ የምታሰጋ፣ ጎጠኝነት እራቁቷን ያስቀራት፣ ኢትዮጵያዊ ነኝ የሚል ትምክህተኛ ሆኖ የሚፈረጅባት የመከራን ቁልቁል የምትጋልብ ሀገር ሆናለች ኢትዮጵያ፡፡
4 ብሄራዊ መግባባት የጠፋባት፣ ሌላውን ላለማስገባት ሁሉም በሩን የዘጋበት፣ የሀገር ትርጉም የጠፋባት፤ ስለ ሀገር ሲጠየቅ ‹‹ምን አገባኝ›› የሚልን ተረት ተናጋሪ የበዛባት ሀገር ሆናለች ኢትዮጵያ፡፡
5 ተቃዋሚ ፓርቲዎች ከራሳቸው ጋር መታረቅ አቅቶቸው አብሮቸው እየሮጠ ያለውን ጠልፈው የሚጥሉባት፣ ተገረፍን ታሰርን እያሉ በሰበብ አስባቡ አገር የሚለቁባት፡፡ ከዚህም የተነሳ ለውጥ ፈላጊው ህዝብ የተቃውሚ ፓርቲዎችን ጭመር በጥርጣሬ የሚያይባት፡፡ ለተቃዋሚም ለመሪም ያልታደለች፣ የመንግስት ለውጥ እንጂ እውነተኛ ለውጥ ያልሰመረላት አገር ኢትዮጵያ፡፡
…..ዛሬም ልጆቿ ይታሰራሉ፣ያለከልካይ ከቦታቸው ይፈናቀላሉ፣ ይደበደባሉ አካላቸው ይጎላል፡፡ሙስና የመጨባበጥ ያህል የቀለለባት፣ከደሀ 10 ካ.ሜ ተነጥቆ ለባለ ገንዘብ 10,000 ካ.ሜ የሚሰጥባት፡፡
ዜግነት በገንዘብ እና በአሸርጋጅነት (በተለጣፊነት) የሚከበርባት ሆናለች ሀገሬ ኢትዮጵያ፡፡
ታዲያ ይሄን ኧረ ማን ይናገርላት????????
ከ95% የማያንሰው የሀገራችን ህዝብ እንኳን ሶሻል ሚዲያ ሊጠቀም ይቅርና ሶሻል ሚዲያ ማለት ምን ማለት እንደሆነ እንኳን ለማወቅ ያልታደለ ነው፡፡ ታዲያ 5% የማይሞላ የሶሻል ሚዲያ ተጠቃሚ ባለባት ሀገር ውስጥ እንዴት ነው ሀገር በሶሻል ሚዲያ የምትተራመሰው? የምር ያስቃል፡፡
ከሰብኣዊ
Wednesday, April 30, 2014
Saturday, April 26, 2014
ስድስት የዞን 9 ጦማርያን በመንግሥት ተያዙ
Added by webteam on April 25, 2014
ዛሬ አርብ ሚያዝያ 17 ቀን 2006 አመሻሹ ላይ 11፡20 ገደማ ስድስት የዞን ዘጠኝ ጦማርያን አባላት ናትናኤል ፈለቀ፣ በፍቃዱ ሀይሉ፣ አጥናፍ ብረሀነ፣ ማህሌት ፋንታሁን፣ ዘላለም ክብረት እና አቤል ዋበላ በመንግስት የጸጥታ ሀይሎች ከያሉበት ተይዘዋል፡፡ ይህንኑ ዜና ይፋ ያደረገው የጦማሪያኑ የፌስቡክ ገጽ ሲሆን፤ ታሳሪዎቹን ለመያዝ የመጡት አካላት የማሰሪያና የመፈተሻ የፍርድ ቤት ፈቃድ የያዙ መሆናቸውን መስማታቸውን በዚሁ አጭር መግለጫ ላይ ተጠቅሷል።
ከሰአታት በፊት በወጣው መግለጫ፣ ““ዞን 9” የጦማርያን ስብስብ አባላት ሚያዚያ 15፣2006 በዋጣነው መግለጫ ላለፉት ሰባት ወራት የዞኑ አባላት ከፍተኛ የሆነ ክትትል ሲደረግባቸው እንደነበር በጠቅላላው የተጠቆመ ሲሆን ክትትሉ የተወሰኑ የቡድኑን አባላትና የቅርብ ወዳጆችን ጭምር ያካተተ ነበር፡፡ አሁን በመንግስት የተወሰደው እርምጃ የዞኑን ተመልሶ ወደ ስራ መግባት ተከትሎ ሊሆን እንደሚችል ይገመታል ሆኖም የዞን 9 አባላትና ወዳጆች በምንም አይነት ህገ ወጥ ተግባር ላይ ተሰማርተው እነዳልነበር ለማረጋገጥ እንወዳለ፡፡” በማለት ያትታል።
በተያያዘ ዜና ጋዜጠኛ ተስፋለም ወልደየስም ዛሬ በፀጥታ ሀይሎች ቁጥጥር ስር መግባቱም ተዘግቧል።
ይህ ዜና እስከተጠናከረበት ጊዜ ድረስ በመንግስት በኩል የተሰጠ ምንም አይነት ማብራሪያ የለም።
Category:
ArticlesTags:
abel wabela, amharic news, atnaf berhane, befekadu hailu, ethiopia, ethiopian news, ethiotube, mahlet fantahun, natnael feleke,zelalem kibret, zone9, zone9ersThursday, April 24, 2014
ሰበር ዜና- ፖሊስ ቀስቃሾቹን እያሰረ ነው ፖሊስ የእውቅናው ደብዳቤ አልደረሰኝም በሚል በተለያዩ የአዲስ አበባ ክፍሎች ቅስቀሳ ላይ የተሰማሩትን የሰማያዊ ፓርቲ አባላትና ደጋፊዎች እያሰረ ነው፡፡ April 24/2014
ሰበር ዜና- ፖሊስ ቀስቃሾቹን እያሰረ ነው ፖሊስ የእውቅናው ደብዳቤ አልደረሰኝም በሚል በተለያዩ የአዲስ አበባ ክፍሎች ቅስቀሳ ላይ የተሰማሩትን የሰማያዊ ፓርቲ አባላትና ደጋፊዎች እያሰረ ነው፡፡
April 24/2014
ፖሊስ ቀስቃሾቹን እያሰረ ነው ፖሊስ የእውቅናው ደብዳቤ አልደረሰኝም በሚል በተለያዩ የአዲስ አበባ ክፍሎች ቅስቀሳ ላይ የተሰማሩትን የሰማያዊ ፓርቲ አባላትና ደጋፊዎች እያሰረ ነው፡፡ በአሁኑ ወቅት በየካ፣ ካሳንቺስና አቧሬ ሲቀሰቅሱ የነበሩ ወጣቶች በፖሊስ ተይዘው ታስረዋል፡፡ ቀስቃሾቹ ሰልፉ እውቅና እንደተሰጠው የሚያመለክተውን ወረቀት ለፖሊስ ቢያሳዩም ፖሊሶች የእውቅናው ደብዳቡ አልደረሰንም በሚል አስረዋቸዋል፡፡ ቀስቃሾቹ የያዙት የእውቅና ደብዳቤ ግልባጭ ለፖሊስ የተጻፈበት በመሆኑ ሰልፉ እውቅና አግኝቶ እያለ ሆን ተብሎ ለማደናቀፍ እንደሆነ ምክትር ሊቀመንበሩ አቶ ስለሽ ፈይሳ ገልፀዋል፡፡
በላም በረት፣ ቦሌ ድልድይ፣ ኮተቤ፣ መገናኛ ቅስቀሳ ሲያደርጉ የነበሩ የሰማያዊ ፓርቲ አባላትና ደጋፊዎች ቅስቀሳቸውን በተሳካ መልኩ አጠናቀዋል፡፡ በሌሎች አካባቢዎች የተሰማሩት አባላት ቅስቀሳውን አጠናክረው ቀጥለዋል፡፡ በሌላ በኩል በየካ፣ ካሳንቺስና አቧሬን ጨምሮ በሌሎች የከተማይቱ ክፍሎች ፖሊስ ከ20 በላይ አባላትን ማሰሩ ታውቋል፡፡
ሰበር ዜና ፖሊስ ቅስቀሳው ላይ ያልነበሩ የሰማያዊ ፓርቲ አመራሮችንም እያሰረ ነው፡፡ የታሰሩትን አባላትና ደጋፊዎች ሁኔታ ለማጣራት ወደ የካ ፖሊስ ጣቢያ ያቀኑ የሰማያዊ ፓርቲ አመራሮችና አባላትን ፖሊስ አስሯቸዋል፡፡
በዛሬው ቀን ካሳንቺስ ስድስተኛ ፖሊስ ጣቢያ የታሰሩት
1. ብሌን መስፍን
2. አስናቀ በቀለ
3. መስፍን
4. ተስፋዬ አሻግሬ
5. እዮብ ማሞ
6. ኩራባቸው
7. ተዋቸው ዳምጤ
የካ ፖሊስ ጣቢያ ታስረው የሚገኙት የሰማያዊ ፓርቲ አባላትና ደጋፊዎች
1. ፍቅረ ማሪያም አስማማው
2. እያስፔድ ተስፋዬ
3. ጋሻው መርሻ
4. ተስፋዬ መርኔ
5. ሀብታሜ ደመቀ
6. ዘሪሁን ተስፋዬ
7. ጌታነህ ባልቻ
8. ንግስት ወንዲፍራው
9. ሜሪን አለማየሁ ናቸው
የካ አካባቢ ታስረው የሚገኙ የሰማያዊ ፓርቲ አመራሮችና አባላት ምግብ እንዳይገባላቸው ተከልክለዋል፡፡ በሌላ በኩል አህመድ መሃመድ፣ሀይለማሪያም፣ ሱራፌልና አምሃ የተባሉ የሰማያዊ ፓርቲ አባላት መገናኛ አካባቢ ተይዘው ወደ የካ ፖሊስ ጣቢያ ተዘዋውረዋል፡፡ በአጠቃላይ የካ ፖሊስ ጣቢያ የሚገኙት 14 መሆናቸው ታውቋል፡፡ በሁሉም ፖሊስ ጣቢያዎች የሚገኙት አመራሮችና አባላት በአሁኑ ወቅት ቃል እየሰጡ ሲሆን ሊያድሩ እንደሚችሉም ተነግሯቸዋል፡፡
በሌላ በኩል የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን ምክትል ኮሚሽነር ቢሮ ተደውሎ የሰላማዊ ሰልፉን አስተባባሪዎች ጧት ሁለት ሰዓት ላይ ‹‹ኑ እና እንነጋገር!›› የሚል ጥሪ አድርጓል፡፡ ከሰልፉ አስተባባሪዎች መካከል አቶ ጌታነህ ባልቻ ታስሮ ይገኛል፡፡
ፖሊስ ቀስቃሾቹን እያሰረ ነው ፖሊስ የእውቅናው ደብዳቤ አልደረሰኝም በሚል በተለያዩ የአዲስ አበባ ክፍሎች ቅስቀሳ ላይ የተሰማሩትን የሰማያዊ ፓርቲ አባላትና ደጋፊዎች እያሰረ ነው፡፡ በአሁኑ ወቅት በየካ፣ ካሳንቺስና አቧሬ ሲቀሰቅሱ የነበሩ ወጣቶች በፖሊስ ተይዘው ታስረዋል፡፡ ቀስቃሾቹ ሰልፉ እውቅና እንደተሰጠው የሚያመለክተውን ወረቀት ለፖሊስ ቢያሳዩም ፖሊሶች የእውቅናው ደብዳቡ አልደረሰንም በሚል አስረዋቸዋል፡፡ ቀስቃሾቹ የያዙት የእውቅና ደብዳቤ ግልባጭ ለፖሊስ የተጻፈበት በመሆኑ ሰልፉ እውቅና አግኝቶ እያለ ሆን ተብሎ ለማደናቀፍ እንደሆነ ምክትር ሊቀመንበሩ አቶ ስለሽ ፈይሳ ገልፀዋል፡፡
በላም በረት፣ ቦሌ ድልድይ፣ ኮተቤ፣ መገናኛ ቅስቀሳ ሲያደርጉ የነበሩ የሰማያዊ ፓርቲ አባላትና ደጋፊዎች ቅስቀሳቸውን በተሳካ መልኩ አጠናቀዋል፡፡ በሌሎች አካባቢዎች የተሰማሩት አባላት ቅስቀሳውን አጠናክረው ቀጥለዋል፡፡ በሌላ በኩል በየካ፣ ካሳንቺስና አቧሬን ጨምሮ በሌሎች የከተማይቱ ክፍሎች ፖሊስ ከ20 በላይ አባላትን ማሰሩ ታውቋል፡፡
ሰበር ዜና ፖሊስ ቅስቀሳው ላይ ያልነበሩ የሰማያዊ ፓርቲ አመራሮችንም እያሰረ ነው፡፡ የታሰሩትን አባላትና ደጋፊዎች ሁኔታ ለማጣራት ወደ የካ ፖሊስ ጣቢያ ያቀኑ የሰማያዊ ፓርቲ አመራሮችና አባላትን ፖሊስ አስሯቸዋል፡፡
በዛሬው ቀን ካሳንቺስ ስድስተኛ ፖሊስ ጣቢያ የታሰሩት
1. ብሌን መስፍን
2. አስናቀ በቀለ
3. መስፍን
4. ተስፋዬ አሻግሬ
5. እዮብ ማሞ
6. ኩራባቸው
7. ተዋቸው ዳምጤ
የካ ፖሊስ ጣቢያ ታስረው የሚገኙት የሰማያዊ ፓርቲ አባላትና ደጋፊዎች
1. ፍቅረ ማሪያም አስማማው
2. እያስፔድ ተስፋዬ
3. ጋሻው መርሻ
4. ተስፋዬ መርኔ
5. ሀብታሜ ደመቀ
6. ዘሪሁን ተስፋዬ
7. ጌታነህ ባልቻ
8. ንግስት ወንዲፍራው
9. ሜሪን አለማየሁ ናቸው
የካ አካባቢ ታስረው የሚገኙ የሰማያዊ ፓርቲ አመራሮችና አባላት ምግብ እንዳይገባላቸው ተከልክለዋል፡፡ በሌላ በኩል አህመድ መሃመድ፣ሀይለማሪያም፣ ሱራፌልና አምሃ የተባሉ የሰማያዊ ፓርቲ አባላት መገናኛ አካባቢ ተይዘው ወደ የካ ፖሊስ ጣቢያ ተዘዋውረዋል፡፡ በአጠቃላይ የካ ፖሊስ ጣቢያ የሚገኙት 14 መሆናቸው ታውቋል፡፡ በሁሉም ፖሊስ ጣቢያዎች የሚገኙት አመራሮችና አባላት በአሁኑ ወቅት ቃል እየሰጡ ሲሆን ሊያድሩ እንደሚችሉም ተነግሯቸዋል፡፡
በሌላ በኩል የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን ምክትል ኮሚሽነር ቢሮ ተደውሎ የሰላማዊ ሰልፉን አስተባባሪዎች ጧት ሁለት ሰዓት ላይ ‹‹ኑ እና እንነጋገር!›› የሚል ጥሪ አድርጓል፡፡ ከሰልፉ አስተባባሪዎች መካከል አቶ ጌታነህ ባልቻ ታስሮ ይገኛል፡፡
Wednesday, April 23, 2014
የወያኔዎች አስቂኝ መመሪያዎችና ዐዋጆች
April 23, 2014
ነፃነት ዘለቀ (ከአዲስ አበባ)
በመጀመሪያ የክርስትና እምነት ተከታይ አንባቢዎች እንኳን ለ2006ዓ.ም የትንሣኤ በዓል በሰላም አደረሳችሁ፡፡
ሕወሓት ወደ ሥልጣን መጥቶ በዓይነቱ የተለዬ የጥቁር አፓርታይድ ሥርዓትን በዓለማችን ለመጀመሪያ ጊዜ በኢትዮጵያ ካቆመ ወዲህ እጅግ ብዙና ለመቁጠርም የሚያዳግቱ መመሪያዎችንና ዐዋጆችን ቀርፆአል፡፡ አንዳንዶቹን በዘፈቀደና በነሲብ እየቸከቸከ በፈለገው ሰዓትና ወቅት ራሱ ተግባራዊ በማድረግ፣ አንዳንዶቹንም ለማስመሰል ያህል በእንቅልፋምና ደናቁርት የ“ፓርላማ” አባላቱ አማካይነት በዐይን ጥቅሻ በሚታዘዝ የሆዳም ማይማን ጭብጨባ “አጸድቆ” ሥራ ላይ በማዋል ሀገርንና ሕዝብን ማተራመስ ከያዘ ሁለት ዐሠርት ዓመታትን ጨርሶ የሦስተኛውን ዐሠርት አንድ ሦስተኛ ያህል ጊዜ ለማገባደድ ጥቂት ወራት ብቻ ይቀሩታል፡፡
ከቅርቦች ልጀምር፡፡ ቅድም ቡና ስጠጣ እንዲህ የሚል ወሬ ሰማሁ፡፡ እውነት ይሁን ሀሰት ገና አላረጋገጥሁም – ይሁን እንጂ የወያኔን ባሕርይ ለሚያውቅ ይህን ወሬ ሀሰት ነው ማለት የሚያስችል አዲስ ነገር አይገኝም፡፡ ከዚህ የበላለጡ አስቂኝና አስገራሚ መመሪያና ዐዋጆችን እየታዘብን 23 የመከራና ፍዳ ዓመታትን ስላቀናን ይህኛውን የተለዬ አያደርገውም፡፡ የሰማሁት ምን መሰላችሁ – ልማታዊ የወያኔ ሙዚቀኞችና ዳንኪረኞች በኮፒራይት መቸገራቸውን ስላመለከቱና ለዚህም ችግር መባባስ ትልቁን ሚና እየተጫወቱ የሚገኙት የስልኮች ሚሞሪዎችና ብሉቱዝ በመሆናቸው እነዚህን አገልግሎቶች የሚሰጡ ማናቸውም የቴክኖሎጂ ውጤቶች ወደ ሀገር እንዳይገቡ መንግሥት ማገጃ አውጥቷል የሚል ነው፡፡ በዚህም ሳቢያ የእጅ ስልኮችና የመሳሰሉት የኤሌክትሮኒክስ ዕቃዎች ማዕቀብ ሊጣልባቸው እንደሆነ እየተነገረ ነው፡፡ ለነገሩ ከኢትዮጵያ የወያኔ ሚዲያዎች በውዴታየ ስለራቅሁ ይህ መመሪያ በገሃድ ወጥቶ ይሁን አይሁን እስካሁን አላወቅሁም፡፡ በበዓሉ ምክንያት ከጎረቤት ውጪ ራቅ ወደሚል ሌላ ውጪ አልወጣሁም፡፡ ግን አይሆንም አይባልም፡፡ ወያኔ ከፈለገ “ከዛሬ ጀምሮ ከትግሬ በስተቀር ነጭ ጤፍ እንጀራ የሚበላና ጮማ የሚቆርጥ ሌላ የማኅበረሰብ ክፍል እንዳይኖር ዐውጃለሁ፤ ቢኖር ግን ህገ መንግሥቱን በኃይል ለመናድ እንደቃጣ ተቆጥሮ በአሸባሪነት የክስ ቻርጅ እስከሞት ሊደርስ በሚችል ከፍተኛ ቅጣት ዋጋውን ያገኛል፡፡” ብሎ ሊያውጅ ይችላል፡፡ ማንን ወንድ ብሎ ነው ወያኔ የፈለገውን ከማድረግ የሚቆጠበው? ወያኔ በምን ይዳኛል? በምንም፡፡ ለነገሩ ቀን የሰጠው ጅብ አንበሣንና ነብርን ሲቆረጣጥም ቢታይ ዘመኑ የትንግርት ነውና አያስገርምም፡፡ በኢትዮጵያም ሆነ በተቀረው ዓለም እየሆነ ያለውም ይሄውና ይሄው ብቻ ነው፡፡ ግን ግን በሀገራችን ለወደፊቱ ጅብ የማያሸንፍበትን ቀዳዳ መዝጋት የሚያስችለንን ታላቅ የሦስተኛው ሚሌንየም ሥልት መንደፍ እንደሚገባን ከወያኔው አዋራጅ የተፈጥሮ ልክስክስ ጠባይ የተማርን ይመስለኛል፤ የመንጌን አማርኛ ልጠቀምና ብታምኑም ባታምኑም የአፄውና የደርጉ ሥርዓቶች መንገዱን ባበጃጁለት ወያኔ ክፉኛ ተዋርደናል፡፡ አሸንፎ የማያውቅ ትንሽ ሰው እንዳያሸንፋችሁና መሣቂያና መሣለቂያ እንዳያደርጋችሁ በርትታችሁ ጸልዩ፡፡ ትንሽ ስል ማሸነፍን እንደህልም ይቆጥር የነበረ የባንዳዎችና የሥነ ልቦና ደዌ የተጣባቸው በበቀልና ጥላቻም የተሞሉ ዜጎች ውላጅ የሆኑ መለስን፣ ስብሃትንና ሣሞራን የመሰሉ የታሪክ አራሙቻዎች ማለቴ ነው፡፡ እንደነዚህ ያሉ ቀላሎች በታሪካዊ መደላድሎች መመቻቸት ምክንያት አንዳች ዕድል ካገኙ እንዴቱን ያህል ወጥ እንደሚረግጡና ነገሮችን በምን ያህል ደረጃ እንደሚያበለሻሹ በሚገባ ተረድተናል፡፡ ለማንኛውም ሚሞሪ ያላቸው ስልኮችና መሰል ጋጄቶች ሊከለከሉ ነው አሉ፡፡ አልጋህ ውስጥ ተደብቀህም በሙዚቃ መቆዘም ሊቀር ነው፡፡ ኧረ ባል በሚስቱና ሚስትም በባሏ ቀረጥ እንዳይከፍሉ ያሰጋል፡፡ “እያንዳንድሽ ማን በሚገዛው ሀገር ውስጥ ተኝተሸ ዓለምሽን ትቀጫለሽ?” ብሎ ምቀኛው ወያኔ ለአንድ ግንኙነት ብር 50 ግብር ቢጥልና በየጉያችን ኤሌክትሮኒክ ሥውር ባልቦላ(ማይክሮቺብስ) እንደኖር ፕላንት ቢተክል ባለትዳሮች ምን ይውጠናል? ያቺው ብቸኛ መዝናኛችን ላይ ወያኔ በመብረቃዊ የማጥቃት እርምጃው ቢዘምትባት ወዴትና ለማንስ አቤት እንላለን? የሰይጣን ጆሮ ይደፈን፡፡ የምንተነፍሰውን አየርና የፀሐዩንማ በኑሮ ውድነቱ ላይ ጨምሮ ባልተወለደ አንጀት እያስገፈገፈን ነው፡፡
ከውጭ ሀገራት በበርሜል ዕቃ ማስገባት ተከልክሏል፡፡ በካርቶንና በከረጪት እንጂ በርሜል አይገባም፡፡ ምክንያቱን መጠየቅ አያስፈልግም፡፡ ሊሆን የሚችለው ብቸኛ ምክንያት አንዱ ወያኔ ትግሬ – አንዱ ዘመነኛ በጥጋብ የተወጠረ ትግሬ ወያኔ – የበርሜል ፋብሪካው ገበያው ቀንሷል ማለት ነው፡፡ ለዚህ መፍትሔው ደግሞ ቀላል ነው፡፡ ማታ ሼራተን ወይ ሂልተን ላይ ለሚጋብዛቸው ወያኔ ተጋዳላዮች ለአንዱ ሹክ ማለት ነው – “ከነገ ጀምሮ ከዐረብም ይሁን ከሌላ ሀገር የበርሜል ዘር በቦሌም ይሁን በባሌ ወደኢትዮጵያ ሕዝቦች መኖሪያ ክልሎች እንዳይገባ ጥብቅ መመሪያ አውጣልኝ፡፡” በቃ፡፡ ይቺ ትዕዛዝ ብቻ በቂ ናት፡፡ ከማግስቱ ጀምሮ በርሜል ይቅርና አንዲትም የላስቲክና የብረት ኩባያ ወደሀገር እንዳትገባ ማድረግ ነው፤ ለወያኔዎች ይህን ማድረግ ቀላል ነው፡፡ ሣተናዎቹ ወያኔዎች የፈለጉት ይሆናል፤ ያልፈለጉት አይሆንም – ዘጠና ሚሊዮን ሕዝብ አንቀጥቅጠው መግዛት የቻሉ የአጋንንት ወኪሎች በመሆናቸው ለጊዜው የሚያቅታቸው ነገር የለም፡፡ ይህንን ደግሞ ዕንወቅ፡- እነዚህ ሽል መንጣሪ ዘረኛ የሣጥናኤል ልጆች ከራሳቸው የሚወጣ አንዳችም ኃይል የላቸውም፤ ኃይላቸው የኛ ክፋት፣ የኛ ብዙ ክፋት ነው፡፡ (ለምሳሌ አሁን አንቺ ለኔ መልካም ታስቢያለሽ? ካሰብሽልኝ እሰዬው – ካልሆነ ግን አሁኑኑ ጀምሪውና ሞክሪው፡፡) አዎ፣ በርግጥም ክፉዎች ነን፡፡ በክፋታችንና በአመፀኝነታችንም ሰበብ እያገኘን ያለነውን እያገኘን ነን – በኢትዮጵያ ውስጥ ብቻም ሣይሆን በመላው ዓለም ዙሪያ፡፡ እንጂ እነዚህ የት እንዳሉ እንኳን የማይታወቁ ‹ረቂቅ› ጠላቶቻችን ይህን ሁሉ ሚሊዮን ሕዝብ እንዲህ ኮድኩደው ባላሰቃዩት ነበር፡፡ ወደኅሊናችን ብንመለስ፣ ብንደማመጥ፣ ቁስላችንን ብንመለከት፣ የተፋፋቅነውንና የተጋጋጥነውን በጋራ ለማከም – ለመተካከም- ብንቆርጥ….. እውነቴን ነው የምለው ችግራችንን ለማስወገድ ጥቂት ወራት ብቻ በበቁን፡፡ ግን ብዙዎቻችን በአሉታዊነት የተጠመቅን፣ የክፋታችን ክርፋት ቀድሞን አካባቢን በመጥፎ ጠረን የሚበክል፣ በአስመሳይነትና በሥልጣን ጥም የታወርን፣ በንቀትና በትዕቢት ተወጥረን በጥላቻ ገመድ አንዳችን አንዳችንን የምንጠልፍ፣ በመታች ደብተራና በአባይ ጠንቋይ ድቤ መቺ አበጋር በሰው ላይ እያስመተትንና እያስተበተብን የተቀየምናቸውን ወይም የተመቀኘናቸውን ሰዎች የምናሳብድና የምናደኸይ፣ ለአገዛዝ እንዲያመቸን ብዙኃኑን ዜጎች በማይምነት ጥቁር መጋረጃ ሰነካክለንና በማይረባ የትምህርት ሥርዓት ወጣት ትውልድን አደንቁረን የምናስቀር፣ በሚዲያና በወረቀት ላይ ያልሠራነውን እንደሠራን እያስመሰልን የውሸት ልቃቂት የምንተረትርና የሀሰት እስታትስቲክስ በየዋሃን ዜጎች ጆሮ ዙሪያ የምናዳውር፣ ከጥረት ይልቅ በሰይጣናዊ መንገድና በሙስና በአቋራጭ እንዲያልፍልን የምንሞክር ግብዞችና አንዳችን ለሌላኛችን የማንተኛ ሸፍጠኞች … በመሆናችን የምናስበውን ከመፈጸማችን በፊት ልብንና ኩላሊትን የሚመረምር አምላከ ኢትዮጵያ ስንኩል ዕቅዳችንንና በራስ ወዳድነት ላይ የተመሠረተ አጥፊ ሤራችንን አስቀድሞ የእምቧይ ካብ ያደርገዋል – ይህን ነገር ‹ሀሰት ነው› ብለህ የምትሞግተኝ ካለህ ወደ ኢትዮጵያ ምጣና ተጨባጩን ማኅበረሰብኣዊ ተራክቦ ተመልከት፤ ከዚያም “አሃ፣ እውነትም ወያኔም ሲያንሰን ነው ለካንስ” ብለህ ልትፈርድ ትችላለህ – ይህንን እነሱም ያውቁታል፤ እኛም እናውቃለን፤ ፈጣሪም ያውቀዋል፤ ሰይጣንም ሣይቀር በሚገባ ያውቀዋል – የክፋት ሠራዊት አባላት ግና ጊዜያቸውን በደንብ እንደሚጠቀሙበት የታወቀ ነውና ካለሰዓቱ ንቅንቅ አይሉም፤ ጅብ የጎረሰውን እያላመጠ ይሞታታል እንጂ እየሞተም ቢሆን መብላቱንና ግዳይ መጣሉን በተስፋ መቁረጥ ምክንያት አይተውም፡፡ የሚመር አውነት ነው፡፡
በሳይጋገር ተቦካና በላም አለኝ በሰማይ ገና ለገና ሥልጣን ተገኝቶ፣ ገና ለገና ወያኔ ወድቆ፣ ገና ለገና በሀገር ላይ “ዴሞክራሲ” ‹ሰፍኖ›፣ ገና ለገና ከአንበሣ አፍ ሥጋ ወድቆ ለጅብ ተርፎ … ተቃዋሚዎቻችን የሚያሳዩትን የርስ በርስ መጠላለፍና የሚያካሂዱትን ዶንኪሾታዊ ፍልሚያ እንኳን አታይም? ከዚህ አንጻር ውጥንቅጡንና አስጠሊታውን የታሪካችንን ገጽታ ስናይ በመቶዎችና በሺዎች በሚገመቱ የፖለቲካና ማኅበረሰባዊ ኩይሣዎች እየተቧደንን በሁለንተናዊ የሥነ ልቦናና አካላዊ ጦርነት ለዘመናት መፈሳፈሳችን የወያኔን ተልእኮ ስኬታማነት ለማረጋገጥ ከማገዛችን ውጪ የትም ልንደርስ አልቻልንም፤ ያማረ ንግግር፣ ያማረ የፖለቲካ ፕሮግራምና የተዋበ ፍልስፍናም እንዲሁ የዕውቀታችንን ምጥቀትና የመጻፍ ችሎታችንን ከማሳየት ባለፈ የረዳን ነገር የለም – እንጂ ለምሁር ለምሁርማ ስንት ሺህ ዶክተርና ፕሮፌሰር ሞልቶን አልነበረምን? የጥንት አስተሳሰብ በዘመናዊ ቆዳ ተሸፍኖ በጠበጠን እንጂ ንግግር ዐዋቂና ነገር ሰላቂማ ሞልቶናል፡፡ እናሳ፡- ከእኛ ከኢትዮጵያውያን በላይ ጉዶችና ተዓምረኞች ይገኛልን? “እባብ ልቡን አይቶ እግሩን ነሣው” እንደምንል የብዙዎቻችን ፍላጎት ከአነጋገራችንና ከዐይነ ውኃችን ጭምር ይታወቃል፤ በክፉ አሳባችንም ምክንያት ውጥናችን ሳይጀመር ይከሽፋል፡፡ እናም እንደመፍትሔ ሁላችንም እውነተኞች እንሁን፤ ማስመሰልን እንጠየፍ፤ ለወገናችን የዓዞን ሣይሆን ለልጇ ስትል እንደተወጋችው ጎሽ ከአንጀት እናልቅስ፤ ከዘረኝነትና ጎጠኝነት አረንቋ ባፋጣኝ እንውጣ፤ ያለንበትን ዘመን እንረዳ፡፡ ወገናችንን እንውደድ – እናፍቅርም፤ ሀገራችንንና ሕዝባችን የምንለውን ወገናችንን ለሥልጣን መወጣጫነት ሣይሆን በሀቅ ወደን እስከሕይወት መስዋዕትነት ትልቅ ዋጋ በመክፈል ከገቡበት አዘቅት እናውጣቸው፡፡ ያኔ ነው ፈጣሪ የሚባርከንና ዕቅዳችንን ቀድሶ በተገቢው መንገድ እውን የሚያደርግልን፡፡ አለበለዚያ ወያኔ አሁን እንደሌለ ሁሉ በሌለበት ሁኔታ አገዛዙን በእጅ አዙር ቀጥሎ የመለስና የመሪ ድርጅቱ የወያኔ አፅም ጉድጓድ ውስጥ ሆነው በሹምባሾቻቸው አማካይነት እስከወዲያኛው እያንቀጠቀጡ ይገዙናል – ልብ አድርጉ የሚገዛን ግን የወያኔ ጥንካሬ ሣይሆን የኛ ልፍስፍስነትና የኛ መጥፎ ሃሳብ ካርማዊ ዕድፍ የሚያጠላብን የመርገምት ውጤት ነው፡፡ አሁንና እስካሁን አንድ ያላደረገን የተለያየው ፍላጎታችን እንጂ የሚደርስብን ግፍና በደል ተለያይቶ እንዳልሆነ ይታወቃል፡፡ እስከዚህን ደረጃ ያለያየን ለምንም ዓይነት ሕዝባዊ ስቃይ ሊንበረከክ ያልቻለው ግላዊ የሥልጣንና የሀብት ፍላጎታችን እንጂ በርግጥም በእውነት ተለያይተን እንዳልሆነ ኅሊናችን ያውቀዋል፡፡ (በሰላም ቀን የሀገራችን ልዩ መመኪያ ሊሆናት ይችል የነበረውና በሥልጣንና ሀብት አራራው ምክንያት ግን የወያኔ ሥውር ወኪል (mole/double agent) ሆኖ ሀገሩን በክፉ ቀን ከድቶ ከጠላቶቿ ጋር ያበረው ልደቱ አያሌው እንዲያ በመንታ እያነባ ለኢትዮጵያና ሕዝቧ “ሕይወቱን” እስከመሰዋት በሚደርስ “ጽናት” ዝዋይና ሸዋሮቢት የተንከራተተው ለማንና ለምን እንደሆነ በተለይ አሁን ላይ ቁልጭ ብሎ ይታየናልና ከዚህ ዓይነቱ ቁጭ በሉ አስተሳሰብና ዕኩይ ድርጊት በቶሎ እንውጣ፡፡ እውነቴን ነው – በተለይ ከእንግዲህ ማንም ማንንም ሊያታልል አይችልም፡፡ ሁሉም ነቅቷል ፤ ቀኒቷን ግን በጉጉት ይጠብቃል – የነፃነቷን የማትቀር ቀን፡፡) በበኩሌ የወደፊቷ ኢትዮጵያ ለዚህ ዓይነቱ ፖለቲካዊ ድራማ የማትመች እንደምትሆን ተስፋ አለኝ፡፡ አማራ – ትግሬ፣ ኦሮሞ – ሶማሌ …. መባባሉ የታይታና ዘመን ያለፈበት የትግል ስትራቴጂ እንጂ ውስጠ ምሥጢሩ ሌላ መሆኑን እናውቃለን፡፡ ሌላው ልብ ማለት የሚገባ ነገር ደግሞ አራት ኪሎ ቤተ መንግሥት ዘጠና ሚሊዮን ወንበር የለውም፤ አንድ ነው፡፡ ያንንም በዘር ሣይሆን በ‹ሜሪት›ና በሕዝብ እውነተኛ ምርጫ ማስያዝ ይጠበቅብናል – ጊዜው ሲደርስ፡፡… እውነትን ተናግሮ እመሸበት ማደር እንዲህ ይመስለኛል፡፡ ወዳልተነሳሁበት ርዕስ ጥልቅ እያልኩ ማስቸገሬን ይቅርታ አድርጉልኝ፤ ወድጄን እንዳይመስላችሁ፡፡
በዚህ ዘመን ወያኔዎችን “ይህ እኮ ህገ መንግሥታዊ መፍቴ ነው!” ብትል “እሱን ቀቅለህ ከቤተሰቦችህ ጋር ሆነህ ብላው!” ሊሉ ይችላሉ ብቻ ሣይሆን ዘወትር የሚደግሙልህ ውዳሤ ማርያማቸውና መዝሙረ ዳዊታቸው ነው፡፡ ህገ መንግሥቱ – ምን አለፋህ ወንድሜ – የዐዋጁን በጆሮ እንዳትለኝ እንጂ ለአሰለጥ ትግሬዎችና ለፌዴራል የትግሬ ሠራዊት በፍጹም አይሠራም – ሀገርን በቅኝ ግዛት ለወረረ የአንበጣ መንጋ ምክንያታዊነትና ሰብኣዊነት የሚገመዝዘው ቀልድ በመሆኑ ከጠበንጃ ውጪ የሚታየው የችግሮች ማስወገጃ ሌላ ብልሃት ብሎ ነገር የለም፤ ጤናማና ለኅሊናው ተገዢ የሆነ ትግሬ እንደኛው መሰቃየቱን በታሳቢነት ያዝልኝ ታዲያ – ጥቂትም ቢሆኑ አሉ፤ የምን ጥቂት – ብዙ ናቸው ኧረ! እርግጥ ነው ነገሩ ዕንቆቅልሽና ግራ የሚያጋባ ሊመስል ይችላል፡፡ የኢትዮጵያ መንግሥት የሚባለውን የሥልጣን ቦታዎችን፣ የንግድ ተቋማትን፣ የአነስተኛና ጥቃቅን ንግዶችን፣ የሕንፃዎችንና የፋብሪካዎችን ባለቤቶች፣ የመንግሥት ቤቶችን በነፃ ተከራዮችን፣ ኮንዶሚኒየም ቤቶችን፣ የወታደርና የፖሊስ ተቋማትን፣ የደኅንነት መዋቅሩን፣ የባንኩንና የአክሲዮን ሸያጩን፣ ውድ ውድ የሚከፈልባቸው ትምህርት ቤቶችንና ከፍተኛ የትምህርት ተቋማትን፣ መዝናኛ ሥፍራዎችን፣ … በጠቅላላው በሀብቱ ማማ ላይ ፊጥ ያለውንና በትንሹም በትልቁም ሲቆጣ የቀድሞ ወንድምና እህቶቹ የአሁን አሽከሮቹና አጫዋች አኗኗሪዎቹ ላይ፣ የሀብቱም አድናቂዎች የሆኑ ሌሎች ምሥኪን “ወገኖቹ” ላይ በዕብሪት “እቧይ” ሲል የምትሰማውን ትግሬ ስታይ ኢትዮጵያ በአንዳች ትግሬያዊ ምትሃትና ሰሜናዊ ዋግ የተመታች ሊመስልህ ቢችል ዘመኑና አበቅቴው ነውና ቻል ማድረግ ሊኖርብህ ነው፡፡ ኧረ እንዲያውም በተጋቦት ትግሬ የሆነ ሌላ ዜጋም ሲያስመስል “እቧይ!” ሲልና የስልክ መጥሪያውን ካለውዴታው ለማስመሰልና ለመወደድ ሲል ብቻ የትግርኛ አድርጎም ልትታዘብ ትችላለህ፤ አቤት ይህ ጊዜ ሲገርም – ራስን ሲያሳጣና ባዶ ሲያስቀር፡፡ ዘመቻው እኮ ሁለገብ ነው – ኢኮኖሚያዊም፣ ወታደራዊም፣ ሥነ ልቦናዊና ባህላዊም፣ ሃይማታዊም፣ ምናምናዊም ሁሉ ነው፡፡ ታዲያን እንዲህ ያለ ነገር በታሪክ አልፎ አልፎ ሊያጋጥም እንደሚችል “ሚዉቴሽናል ክስተት” በመቁጠር መታገስ ይኖርብናል – ቂሎችን ተከትሎ ቂል መሆንና ለቂም በቀል መነሳሳት አይገባም ብቻ ሣይሆን ቂም በቀል የሚወልደው ሌላ ቂም በቀልንና የዐመፃ ተግባርን በመሆኑ ከዚህ ዓይነት ሃሳብ መታቀብ አማራጭ የሌለው ግዴታ ነው – ከእግዚአብሔር መንገድ የወጡ ሰዎች ከዚሁ የፈጣሪ መንገድ ሊያስወጡን አይገባም – ምንም እንኳን የነሱ ፍላጎት ይሄው ቢሆንም እኛ ግን እነሱ በመጡበት መንገድ በጅልነት ልንማገድበት አይገባንም – ጎጂ ነው፤ ለጊዜው ካልሆነ በዘለቄታዊነት አያዋጣምም፡፡ የአነስታይንን ምክር መቀበል አለብን – “አንድ ችግር በተፈጠረበት የአስተሳሰብ ደረጃ ተጉዞ ችግሩን ማስወገድ አይቻልም፡፡” ክርስቶስም ቀድሞ አለ “ጠላትህን ውደድ፤ አንድ እርምጃ ከእርሱ ጋር እንድትራመድ ቢጠይቅህ ሁለት ድገምለት፤ እጀ ጠባብህን ቢጠይቅህ መጎናጸፊያህንም ድገምለት፤ ግራ ጉንጭህን ቢጠፋህ ቀኝህንም ድገምለት …” ይህ ምክሬ የተለያዩ የትግል አማራጮችን ለሚከተሉ ወገኖች እንደማይጠቅማቸው አውቃለሁና ከነርሱ አንስቻለሁ፡፡ ምርጫን ደግሞ አከብራለሁ – እንደምርጫ፡፡ ይህ አስተያየቴ ተቀባይነት እንዲኖረው የምሻው በተለይ በሃይማኖቱ ማኅበረሰብና በሰላማዊው ሕዝብ መካከል ነው፡፡
አንድ ነገር እንገንዘብ፤ ይህ ጊዜ ዘንጦ ያልፋል፤ ዘንጦ ያላለፈ የክፋት ዘመን በታሪክ እንዳልነበረ ሁሉ ዛሬም አይኖርምና፡፡ በተረፈ ግን እንደውነቱ ከሆነ ይሄ ዘመን ትግሬዎችን አልጠቀመም የሚሉት የጅሎች ፈሊጥ ከፍ ሲል ከገለጽኩት አስቀያሚ ሀገራዊ ገጽታ አኳያ አይገባኝም፡፡ በዚህ ዘመን የማይጠቀም ትግሬ ካለ አእምሮው ጤናማ የሆነና ዛሬ በነገው ቀን ላይ የሚጥለውን ታሪካዊ ዳፋ ከወዲሁ በማጤን አስተሳሰቡን ከአብዛኛው ጭቁን ወገን ጋር ያጣመረ ደግ ትግሬ ብቻ ነው፡፡ ይህ ዓይነቱ ትግሬ እንኳንስ በሌባውና በአጭበርባሪው ወያኔ-ትግሬ በእኛ በኢ-ትግሬያውያኑም ጭምር ሞኝ የሆነ ያህል ይቆጠራል፡፡ ለምን ቢባል ጤናማ አእምሮ በጠፋበትና ይሉኝታቢስነት በነገሠበት የዘረኞች አገዛዝ ውስጥ እንኳንስ ትግሬ የሆነ ሰው ይቅርና የትግሬዎች አንጋችና እግር አጣቢ የሆነ ዜጋ ራሱ ትርፍራፊ መቅቡጥ አያጣምና ነው – ስንቱ የመንደር ካድሬ እንዴት እየተዝመነመነ እንደሚኖር አውቃለሁ፡፡ ኅሊና የሌለው ሰው በአንድ አዳር ከብሮ ሊያድር የሚችልባቸው በሮች በርካታ ናቸው – ወያኔ ደግሞ ለፖለቲካው ሥጋት አትፍጠርበት – ትዛዙንም በጭፍን ተቀብለህ ተግብርለት እንጂ ለጊዜውና እስክትሰባለት ድረስ አያርድህም፡፡ Literally speaking, to my understanding, non-Tigrians are slaves of Tigrians in all denotative and connotative meanings of slavery. Though we cannot differentiate a Tigrian from non-Tigrian especially with respect to color, unlike the case in the apartheidal South Africa or the segregational US, during which the blacks and whites were easily pinpointed, unless maybe by the so called “number 11”, which, again, some non-Tigrians might have it on their temples in their face as well, the difference in life style and possession of wealth between Tigrians and non-Tigrians is absolutely unfathomable. A Tigrian, unless they fear their conscience, can, for example, kill an Amhara in a broad day light and live out of bars. Don’t get surprised, dear sister or brother! There are more severe punishments inflicted upon the Amharas by the TPLF junta, with the blessing of “some” foreign forces, of course. The ‘world’ has been silent, even at times has also been cooperative, and hence, complicit, while Ethiopia and Ethiopians have been suffering for so long, and be sure, everyone will be paid accordingly. Now in Ethiopia, except Tigrians, no one has the right to demand any right that humanity and/or Ethiopian-ness used to give, relatively in abundance, just some decades ago. I think this is the result of animalism from the side of the Tigrians who are ruling, rather, misruling the nation; to my conviction, I do believe that they are missing certain component(s) in their evolution and I can surely say that Ethiopia is currently ruled by a crew of people who have not yet finished their human development in terms of evolution. Could they be homosapiens or australopitecus? I don’t know. But, in reality, the situation is regrettable and pitiful, not necessarily from the vantage point of Stockholm syndrome.
አሁን እንጃ እንጂ አንድም ሹፌር ከጂቡቲ አንዲትም ቡትሌ የምግብ ዘይት ይዞ እንዳይመጣ ተከልክሎ ነበር፡፡ እንደሰማሁት የዛሬን አያድርገውና ከወያኔ ጋር ድብን ያለ ፍቅር ውስጥ የነበረው የጌትአስ ኢንተርናሽናል ካምፓኒ ባለቤት – እልም ያለ ማይም ባለሀብት – ነበር አሉ ያስከለከለው፡፡ ልብ አድርጉ! አንድ የከባድ መኪና ሹፌር በመቀመጫ ወንበሩ ግርጌ ወይ ራስጌ ወትፎ የሚያመጣት አንዲት የ20 ሊትር ጀሪካን ዘይት፣ የዘይት አስመጪውን ሁለገብ ባለሀብት ገበያ ሲሻማበት ይታያችሁ፡፡ ያሳዝናል፡፡ ለዚህ ነው እኛ ኢትዮጵያውያን ምቀኝነትን ከሰውነታችን መንጥሮ የሚያወጣ ፍሪ አንቲቫይረስ ማስጫን እንደሚያስፈልገን ዘወትር ለጓደኞቼ የምናገረው – ማካፌ ወይ አቫስትና ካስፐርስኪ ከተገኙ፡፡ ሀብታሞች ገብጋቦች ናቸው፡፡ ሀብታሞች – በተለይ ኢትዮጵያውያን – የሰው ደም መጣጮች ናቸው – በቀሰምና በስሪንጋ አይደለም – ግን ከዚህ በማይተናነስ የገብጋባነትና ስስታምነት ጭካኔ፡፡ ሀብታሞች ሃይማኖት የሌላቸው – አለን ቢሉም ለይስሙላ ካልሆነ ከልብ የሚያመልኩት አምላክ የሌላቸውና ገንዘብን በርሱም ውስጥ ሰይጣንን የሚያመልኩ- የአጋንንት ማደሪያ ናቸው፤ የጨከንኩባቸው አይመስለኝም፡፡ በምናገረው ጥርጥር የለኝም – ክርስቶስስ ለዚህ ሳይሆን ይቀራል ያቺን የግመልና የመርፌ ቀዳዳ ምሳሌ የተናገረባቸው? በነገራችን ላይ የዚያ ማይም ነጋዴ የአሁኑ ዕጣ በስደት መኖር ነው አሉ – ሰይጣኖች ፍቅራቸውም ጠባቸውም አንድ ነው፤ ሁሉም ነገራቸው ወረትና በህገ ወረትም የሚገዛ ነው፡፡ ሲፋቀሩና ሲጣሉ ጊዜ አይወስድባቸውም – በተለይ በዘር ሐረግ የማይገናኙ ከሆነ፡፡ እንደዚህ ዓይነቱን ቀፎ ሀብታም በልዩ የርቀት መቆጣጠሪያ ነው የሚከታተሉት፡፡ ስለሆነም በሀብት እየበለጣቸው ሲመጣ ተተናኮሉት ማለት ነው – በፖለቲካውስ የሚያገኙት አይመስለኝም፡፡ የርሱ ፖለቲካ እንደከብት በልቶና ጠግቦ ከማደር አያልፍምና፡፡ ይቅርታና ብዙው የወያኔ ጥገኛ ሀብታም በምግብና መጠጥ ከርሱን ከመቀብተትና ከማግሳት እንዲሁም በአጠንካሪ መድሓኒቶች የታገዘ እንትኑን ባገኘው እንትን ሁሉ ከማሾለክ ባለፈ ለሀገር የሚቆረቆረውና የሚጨነቀው ባለሀብት ዜጋ ከቁጥር የሚገባ አይመስለኝም፡፡ የዛሬ ሀብታም እንማንትስ ወርቃለማሁን ጨምሮ በብልግናው ጎዳና መትመምና ባህልንና ወግን ማጨቅየት ከወያም ጋር ካባ እየደረቡ በፍቅር መጫወት እንጂ ለሀገር ማሰቡን ትተውታል፤ ለዚህ ወጣቶቹ ተሸለው ተገኝተዋል፡፡ እነአንዱኣለምንና ርዕዮትን ያስቧል፡፡ ሌላውስ ተከድኖ ይብሰል – ሆዳቸውና እንትናቸው ብቻ አይጉደልባቸው እንጂ የሚሸጥን ሀገራዊ ነገር ሁሉ ይቸበችባሉ፡፡
ሁላችሁም እንደምታወቁት ስዬ አብርሃ፣ በኢትዮጵያ የቀድሞ የዲያብሎስ ባለሙሉ ሥልጣን አምባሳደር መለስ ዜናዊ ሊያውም በጫት ምርቃና አነሳሽነት በደቂቃዎች ውስጥ በተነደፈ የፀረ-ሙስና መሥሪያ ቤት ማቋቋሚያ ዐዋጅ ምክንያት ፍርድ ቤት እንኳን ቢለቀው ለበርካታ ዓመታት እንዲታሰር ተደርጓል፡፡ እንዲህ ናት ኢትዮጵያ! እንዲህ ናቸው ወያኔ ትግሬዎች! የጭንቅላት ችግር ከዚህ በላይ ሊኖር አይችልም፤ ጤናማ የሰውነት ዕድገት ዕጦት ችግር ከዚህ በላይ የለም፡፡ ወያኔ ጋ ፍርድ ቤት የለ፤ ፖሊስ የለ፤ መከላከያ የለ፤ የገንዘብ ሚኒስቴር የለ፤ የውጭ ገበያ የለ፤ የሀገር ውስጥ ገበያ የለ … ሁሏንም ለግላቸውና በግላቸው ተቆጣጥረው መምነሽነሽ ነው፡፡ ይሉኝታ? ከየት ያውቁና! ሀፍረት? የት ያውቁትና! ትዝብት? የት “ገብቷቸው!”፡፡ ግን እንዳይመስላችሁ፡፡ ሁሉንም ያውቁታል፡፡ የመጨረሻ ዕጣ ፋንታቸውን ሳይቀር በሚገባ ያውቁታል፡፡ ክፋትንና መጥፎነትን የመጨረሻ አማራጫቸው ያደረጉት ሌላ አማራጭ በማጣታቸው ይመስላል – ከመነሻው አበላሽተውታልና፡፡ አንዴ ጨክነው ገብተውበታልናም ከአሁን ወዲያ ሌላ በጎ አማራጭ ያላቸው አይመስለኝም፡፡ ለማንኛውም ማሸነፍንና መሸነፍን የማያውቅ አጉል ሰው አያሸንፍህ፡፡ ቀን አይጣልህ ወንድማለም፡፡ ቀን የጣለውን ቀን እስኪያነሳው ያለውን ውጣ ውረድ ለመረዳት ኢትዮጵያዊ ሆኖ መፈጠር ከበቂ በላይ ነው፡፡ ወርቅ በእሳት እንደሚፈተን እኛ ኢትዮጵያውንም በወያኔ-ትግሬ ክፉኛ ተፈተንን፤ አንዳንዶቻችን በፈተናው ወደቅን፤ ጥቂቶቻችን ቢያንስ እስካሁኒቷ ደቂቃ ያሸነፍን መስለን አለን፡፡ ጊዜ በእግዚአብሔር ዘንድ ብዙ ነገር ማለት ነውና የጊዜን የማይዘባበቱበት ፍርድ እንጠብቅ፡፡ ቀኑ ቀርቧል!
የወያኔን ዐዋጆችና መመሪያዎች በሚመለከት ብዙ ማለት ይቻላል፡፡ በእውነቱ እጅጉን ጉደኞች ናቸው፡፡ ሀገር ለመሸጥና ገንዘብ ለማግኘት፣ መኪና ለማስገባት፣ የተወደደ ዕቃ ለማስገባትና ለመሸጥ፣ የሚጠሏቸውን ወገኖች ከገበያ ለማውጣት፣ መሬት ለባዕዳን ለመቸብቸብ፣ ቤትና መሬት ከዜጎች ለመቀማት፣ አንድን ግለሰብ ሳይቀር ለማክበር ወይም ለማደኽየትና ከፈለጉም ዘብጥያ ለማውረድ፣ የፖለቲካና ኢኮኖሚ ተቀናቃኝን ቀንዱን ለመምታት፣ ኑሮን ሰማይ በመስቀል የሕዝብን ቅስም ለመስበርና በዚያውም ሕዝብን የማጀቱ ጣጣ ውስጥ በመወተፍ ሌላ ቁም ነገር እንዳያስብ በማድረግ የበቀል ጥማታቸውን ለማርካት… ወያኔዎች የማንም እገዛና የዓለም አቀፍ ህግ ከለላ ሳያስፈልጋቸው ያሻቸውን ዐዋጅና መመሪያ አውጥተው – እነሱንና ተላላኪ ጭፍራዎቻቸውን ግን ሲያልፍም የማይነካ መሆኑ መታወቅ አለበት – በደቂቃዎች ውስጥ ተግባራዊ ማድረግ ይችላሉ፡፡ በህግ ስም የፈለጉትን እያደረጉ ሀገርንና ሕዝብን እንደገደሉ ቢያንስ እስካሁን ካለተቀናቃኝ ቀጥለዋል፡፡ ነገስ? ነገ ሌላ ቀን ይሆናል፡፡ ሒሳብ ማወራረዳቸውን መጠራጠር አይገባም፡፡
የወያኔን ዐዋጆችና መመሪያዎች በሚመለከት ብዙ ማለት ይቻላል፡፡ በእውነቱ እጅጉን ጉደኞች ናቸው፡፡ ሀገር ለመሸጥና ገንዘብ ለማግኘት፣ መኪና ለማስገባት፣ የተወደደ ዕቃ ለማስገባትና ለመሸጥ፣ የሚጠሏቸውን ወገኖች ከገበያ ለማውጣት፣ መሬት ለባዕዳን ለመቸብቸብ፣ ቤትና መሬት ከዜጎች ለመቀማት፣ አንድን ግለሰብ ሳይቀር ለማክበር ወይም ለማደኽየትና ከፈለጉም ዘብጥያ ለማውረድ፣ የፖለቲካና ኢኮኖሚ ተቀናቃኝን ቀንዱን ለመምታት፣ ኑሮን ሰማይ በመስቀል የሕዝብን ቅስም ለመስበርና በዚያውም ሕዝብን የማጀቱ ጣጣ ውስጥ በመወተፍ ሌላ ቁም ነገር እንዳያስብ በማድረግ የበቀል ጥማታቸውን ለማርካት… ወያኔዎች የማንም እገዛና የዓለም አቀፍ ህግ ከለላ ሳያስፈልጋቸው ያሻቸውን ዐዋጅና መመሪያ አውጥተው – እነሱንና ተላላኪ ጭፍራዎቻቸውን ግን ሲያልፍም የማይነካ መሆኑ መታወቅ አለበት – በደቂቃዎች ውስጥ ተግባራዊ ማድረግ ይችላሉ፡፡ በህግ ስም የፈለጉትን እያደረጉ ሀገርንና ሕዝብን እንደገደሉ ቢያንስ እስካሁን ካለተቀናቃኝ ቀጥለዋል፡፡ ነገስ? ነገ ሌላ ቀን ይሆናል፡፡ ሒሳብ ማወራረዳቸውን መጠራጠር አይገባም፡፡
በሰሞኑ የፋሲካ ገበያ አንዳንድ የአሃዝ ስህተቶችን ከኢሳት ታዝቤያለሁ፡፡ ይህ ስህተት የመረጃ አቀባይ ስህተት ይመስለኛል፡፡ የዕቃዎችና የዓመት በዓሉ ገበያ የዋጋ ዝርዝር አንዳንዱ ትክክል ሆኖ አንዳንዱ ስህተት ነበር፡፡ ስህተት ያልኩት ዋጋው ከእውነቱ የቀነሰ በመሆኑ ነው፡፡ ለምሳሌ የበግ፣የፍሪዳ፣የዶሮ፣ የቅቤ፣ የቀይ ሽንኩርትና የመሳሰሉት ዋጋዎች በኢሳት የተነገረው ከእውነቱ በጣም ቀንሶ ነው፡፡
ሰሞኑን ሁለት ተራራ እሚያህሉ የደለቡ በሬዎች በ90 ሺህ ብር እንደተሸጡ እዚያው የነበረ ሰው አጫውቶኛል፡፡ ዛሬ የበሬ ዋጋ እንዲህ ጥንቡን ጥሎ ለአንድ በጣም የደለበ በሬ ብር 45 ሺህ ተከፈለ እንጂ የዛሬ ዓመት በነበረው የፋሲካ በዓል አንድ በሬ 60 ሺህ ብር መሸጡን ከሁነኛ ሰው በጊዜው ሰምቻለሁ፡፡ 30 ሺህና 20 ሺህማ በብዙ ቦታዎች ተሸጧል፡፡ የምላችሁ እውነቴን ነው፡፡ እያንዳንዳቸው 45 ሺህ ብር የተሸጡት ከብቶች ታዲያ ከውፍረታቸው የተነሣ ወደሚጫኑበት መኪና ለመድረስ የተዘረጋውን የአራት ኪሎ ሜትር ርቀት በእግራቸው ለመጓዝ አንድ ሙሉ ቀን ፈጅተዋል – እያለከለኩና ሊፈርጡ ደርሰው፡፡ 90 ሺህ ብር ሲያነሳቸው ነው አይደል?
ሰሞኑን ሁለት ተራራ እሚያህሉ የደለቡ በሬዎች በ90 ሺህ ብር እንደተሸጡ እዚያው የነበረ ሰው አጫውቶኛል፡፡ ዛሬ የበሬ ዋጋ እንዲህ ጥንቡን ጥሎ ለአንድ በጣም የደለበ በሬ ብር 45 ሺህ ተከፈለ እንጂ የዛሬ ዓመት በነበረው የፋሲካ በዓል አንድ በሬ 60 ሺህ ብር መሸጡን ከሁነኛ ሰው በጊዜው ሰምቻለሁ፡፡ 30 ሺህና 20 ሺህማ በብዙ ቦታዎች ተሸጧል፡፡ የምላችሁ እውነቴን ነው፡፡ እያንዳንዳቸው 45 ሺህ ብር የተሸጡት ከብቶች ታዲያ ከውፍረታቸው የተነሣ ወደሚጫኑበት መኪና ለመድረስ የተዘረጋውን የአራት ኪሎ ሜትር ርቀት በእግራቸው ለመጓዝ አንድ ሙሉ ቀን ፈጅተዋል – እያለከለኩና ሊፈርጡ ደርሰው፡፡ 90 ሺህ ብር ሲያነሳቸው ነው አይደል?
የልጄ ልጅ አቡጡ ጢል አድርጎ የሚያነሳው ኮሳሳ በግ ከ1500 ብር ብዙም አይቀንስም – በጣም የደለበውማ ከአራትና ከአምስት ሺህ ድምቡሎ እንዲቀንስልህ ከፈለግህ ከፋሲካና ከዳግማይ ትንሣኤ ማለፍ አለብህ፡፡ ገበያው እሳት ሆኗል፡፡ ያ በኢሳት የሰማሁት ዘፋኝ “ማገዶ ለቃሚ ምን አደከመሽ፤ ኑሮው እሳት ሆኖ ገብቶ ከቤትሽ” ማለቱ በሥነ ጽሑፍ ቋንቋ እንዴት ያለ ምስል ከሳች መሰላችሁ! በነገራችን ላይ ‹ኢሳት ቲቪ› የማልለው በኢሳት ውስጥ ቲቪ ስላለ ነው፡፡ ኢሳት ሲተረተር ‹የኢትዮጵያ ሣተላይት ቴሌቪዥን› አይደል? በእግረ መንገድ “ድህረ ገፅ” የሚሉ ወገኖቼ “ድረ ገፅ” እንዲሉና ትክክለኛው ይህኛው እንደሆነ ብጠቁም ያስነውረኝ ይሆን? “ድህረ” ሲባል “በኋላ” እንደማለት ነው፤ “ድረ” ማለት ግን “ድር” ከሚለው የሸረሪት ድር ውስጥ የተመዘዘ ሆኖ “ዌብ” የሚለውን የ(እንግሊዝኛ?) ቃል በአማርኛ ለመተካት የተሞከረ ይመስለኛል፡፡ ከተሳሳትኩ ይቅርታ፡፡ እናም ‹ፕሊዝ› “ድረ-ገጽ” ወይም “ድረ-ገፅ” እንበል፤ እናስብልም፡፡
ለማጠቃለል ያህል የ500 ብር ደሞዝተኛና የአምስት ልጆች አባት የሆነው አቶ አዝብጤ ሸዋንግዛው በዚህ የሰሞኑ ፋሲካ የቀረበለት ገበያ በመጠኑ ሲዳሰስ ይህን ይመስል ነበር፡- (ጥራቱን ግን ለአንድዬ ብቻ ሰጥተን ነው ታዲያ – ለምሳሌ ቅቤው አንዱ ጉራንጉር ውስጥ ብልጦቹ ኅሊናአልባ ነጋዴዎች ባላገሮችን ሰብስበው ከምናምን ያለቡት ሊሆን ይችላል – የጥራት ጉዳይ በተለይ በምግብ ነክ አቅርቦቶች ላይ እጅግ አሳሳቢ ደረጃ ላይ ይገኛል፤ በዘይትና ማር እንዲሁም በሌላ ሌላው ሥሪቱ የማይታወቅ የምግብ ግዢ አለማለቃችን የፈጣሪ ረድኤት ታክሎበት ነው እንጂ እንደነጋዴዎቻችን ቢሆን ኖሮ የፈለጉትን በቀጥታ ከአውሮፓና አሜሪካ ከሚያስመጡት ከራሳቸው ከሀብታሞቹና ከባለሥልጣኖቻችን በስተቀር አንድም ሰው በሕይወት ባልተገኘ – አሁን የምንመራው ሕይወታችን በ“ሕይወት አለን” የሚያስብል ከሆነ፡፡) ለማንኛውም ቅቤ ከ170 – 200፣ ዶሮ ከ100 – 280(እኔ 120 ብር የገዛሁት ዶሮ ድስቱ በላው መሰለኝ – እውነቴን ነው የምላችሁ ከዕንቁላሎቹ በስተቀር ጠላታችሁ እልም ይበል ሥጋው ድራሹ ጠፋ! ፈረሰኛ ነው እግረኛ የሚሉት የአባውራ ብልት(የዶሮው አጥንት ማለቴ ነው) ቆዳ ይሁን አንገት መሆኑ ተለይቶ ሳይታወቅ ሟሙቶ አገኘነውና በ“ቆይ ብቻ!” የዘመን መውቀሻ ዛቻ ተሳስቀን አለፍን፡፡ ምን ይደረጋል?)፣ የፈረንጅ ቀይ ሽንኩርት ከ12-17፣ በግ ከ1200 – 5000(+)፣ ምን አለፋችሁ ሁሉም ገበያ ድሃ አይነካሽ ነበር፡፡ የዓመት በዓሉ ብቻ ሣይሆን የአዘቦቱ ገበያም ያው ነው፡፡ ነጋዴው ከማን ጋር እልህ እንደተጋባ ማወቅ አልቻልኩም፡፡ አብዛኛው የኢትዮጵያ ሕዝብ እንዴት ይኖራል? ይህንንም በውል አላውቅም፡፡ ብቻ ይመሻል፤ ይነጋልም፡፡ የሚገርመው ደግሞ መምሸት መንጋቱ ለነሱም ለኛም እኩል መሆኑ ነው፤ ወይ እኛ አናልቅ ወይ እነሱ አይጠረቁ፡፡ ከወያኔ ትግሬዎችና ከአንጋቾቻቸው በስተቀር ሌላው ሰው ሁላ ችግሩን በሆዱ ይዞና ተፈራርቶ መኖርን መርጧል፣ እየኖረ እየመሰለው ግን ሳይኖር ይኖራል፡፡ ሞቶ የሚኖር እንደኢትዮጵያ ሕዝብ የለም እላለሁ፡፡ እንወራረድ! ነገስ? ነገማ ያው ሌላ ቀን ነው፡፡ መልካም ዳግማይ ትንሣኤ፡፡
ህወሓት እስከመቼ ደም ማፍሰሱን ይቀጥላል ? (አቶ ሀብታሙ አያሌው UDJ)
April 23, 2014
ሀገር የመገንጠል ዓላማ ይዞ የተነሳው የህወሓት ጁንታ በስውር እና በአደባባይ የጫካ ልማዱን መሰረት አድርጎ ሲገድል መኖሩ አዲስ ባይሆንም ከሰሞኑ መረር ያለ እርምጃ ‹‹ግድያ›› ማሰቡን ከጓዳው የወጣ የወሬ ምንጭ ደረሰን፡፡ ከጥቂት ደቂቃዎች በፊት በአዲስ አበባ አስተዳደር ጽ/ቤት ተገኝቼ ነበር፡፡ የመገኘቴ ዓላማም የፊታችን እሁድ ሚያዚያ 26 የሚደረገውን ሰላማዊ ሰልፍ አስመልክቶ የዕውቅና ደብዳቤውን ለመስጠት የተያዘውን ቀጠሮ በማክበር ነበር፡፡ የሰላማዊ ሰልፍ እውቅናን በተመለከተ ኃላፊ የሆኑት አቶ ማርቆስ ፎርም እንዲሞላ አዘዙ፤ የተባለውን ፎርም ሞላን፤ ያን ጊዜ የአቶ ማርቆስ የቢሮ ስልክ አንቃጨለ፤ አነሱት ……ቀጭን ትዕዛዝ ከወዲያ ማዶ…………… ‹‹የአንድነትን ሰላማዊ ሰልፍ በተመለከተ ዕውቅናው እንዳይሰጥ ይቆይ›› አቶ ማርቆስ ፊቱ ተለዋወጠ ‹‹ ይቅርታ አድርግልኝ የኔ ችግር አይደለም›› ሌላ ቃል ካፉ አልወጣም፡፡

አልገባኝም ….ቀጠልኩ ….የአንድነት ሰላማዊ ሰልፍ ተከለከለ እያልከኝ ነው ? መለሰ …..እኔ ምን ላድርግ ? …..የከለከለው ማነው የበላይ ኃላፊ ነው ? አዎ አጭር መልስ፡፡ ትቼው ወደ ከንቲባ ጽ/ቤት ኃላፊው አመራሁ፤ ስብሰባ ላይ ናቸው፡፡ ወደ ፓርቲ ጽ/ቤት ደውዬ ሁኔታውን አሳወኩ የፓርቲው ፕሬዘዳንት ኢንጅነር ግዛቸውን ጨምሮ በርካታ አመራሮች ፈጥነው ደረሱ፡፡ የአስተዳደሩ ስብሰባም ለሻይ እረፍት ተቋርጦ ኃላፊው ወደ ቢሯቸው ሲገቡ ተከታትለን ገባን፡፡ ላለማናገር ጥቂት አንገራገሩ የቢሯቸውን በር አንቀን አናግሩን በማለት ጸናን፡፡ ‹‹ምንድነው ችግሩ የሰልፉ ጉዳይ ከሆነ ጨርሰናል፤ እውቅናውን ወሰዳችሁ አይደለም›› ባጭሩ መልስ ተሰጣቸው ፤ አልወሰድንም የአቶ ማርቆስ መልስ ተከልክሏል የሚል ነው፡፡
ጥያቄ አስከተልን ……እርሰዎ መረጃ የለዎትም ? መንግስታዊ ኃላፊነቱ የርስዎ ነው፤ ማነው ከልካዩና ፈቃጁ ? መልስ የለም ጥቂት ዝም ብለው ‹‹የጠየቃችሁን ሚያዚያ 19 ለማድረግ ነበር፡፡ በዚያ ቀን የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን የጥበቃ እጥረት አለብኝ በማለት ስላመለከተ የእናንተ ሰልፍ ለሚያዚያ 26 እንዲደረግ ጠየቅናችሁ ተስማማን ከዚህ ውጪ የተደረገ ነገር ካለ በኔ በኩል መረጃ የለኝም ማን እንደከለከለ አናውቅም›› ስለዚህ ይህንን ከተማ ከንቲባው ካልሆነ ማን ነው የሚመራው? ከወዲያ ማዶ መልስ የለም……….ስልክ አነሱ እና አቶ ማርቆስን ወደ ቢሯቸው ጠሩ ሰውዬው መጡ ማጣሪያ ተጠየቁ መመሪያ ደርሶኛል ሲሉ ለከንቲባው ጽ/ቤት ኃላፊ በኛው ፊት ተናገሩ፡፡ መመሪያ ሰጪው ማነው? ወደ አንዱ ቢሮ ዘው ብለን አንድ ሰው አናገርን ……….. ‹‹እባካችሁ ይቅርባችሁ ደህንነቶቹ የሚውሉት እዚህ ግቢ ነው፡፡ አንድነቶች ከወጡ እርምጃ ይወሰድ ሲሉ ሰምቻለሁ›› አለን በማንሾካሾክ ድምጽ ………….
ጎበዝ ይሙት ሰነፍ ይኑር ቢሻው
አተላ መሸከም ይችላል ትከሻው
ፍርሃት ማነው ቢሉኝ ስሙን አላውቀውም
ሞትን በቁሜ እንጂ ሞቼ አልጠብቀውም፡፡
አተላ መሸከም ይችላል ትከሻው
ፍርሃት ማነው ቢሉኝ ስሙን አላውቀውም
ሞትን በቁሜ እንጂ ሞቼ አልጠብቀውም፡፡
ህወሓት ሊተኩስ ተዘጋጅቷል እኛም የነሱን ጥይት የሚሸከም ደረት …….እመነኝ ካልገደሉ አያቆሙንም፡፡፡
Monday, April 21, 2014
ኢህአዴግን የስለላ መዋቅርና አካሄድ አስመልክቶ እየወጡ ያሉ መረጃዎች ተበራክተዋል። ኢህአዴግ ራሱን እንደሚስለው ዓይነት ድርጅት ሳይሆን በሰብዓዊ መብት አያያዝ ጉድለት ያለበት፣ በሚዲያ ነጻነት ኋላ ቀር፣ የተቃዋሚ ፖለቲከኞችን በማሳደድ ግንባር ቀደም፣ አፋኝ ህግ በማውጣትና በማሸማቀቅ ወደር የማይገኝለት፣ ለሚያወጣው ህግና ደንብ የማይገዛ፣ የውስጥ ችግሩ ታይቶ በማይታወቅ መጠን ዜጎችን ለስደት እየዳረገ እንደሆነ እየተመሰከረበት ነው።
ኢህአዴግን ሸሽተው አገር ለቀው የተሰደዱ በስደት ምድርም ኢህአዴግ እየተፈታተናቸው እንደሆነ መግለጽ ከሰነበቱ ቆይቷል። በአሜሪካ፣ በካናዳ፣ በጀርመን፣ በስዊድንና በእንግሊዝ አገር ስደተኞችን በመሰለል ተግባር ላይ የተሰማሩ “የስደተኛ ሰላዮች” በስፋት ስለመኖራቸው መረጃ ማቅረብ እንደሚችሉ የሚገልጹ ጥቂት አይደሉም። የተለያዩ ድርጅቶች በዚህ ጉዳይ ምን ያህል እንደገፉበት መረጃ ባይወጣም አቶ ኦባንግ ሜቶ የሚመሩት የአዲሲቷ ኢትዮጵያ የጋራ ንቅናቄ ስራውን ያገባቸዋል ከሚላቸው ክፍሎች ጋር እየሰራ እንደሆነ በዚሁ መድረክ መገለጹ ይታወሳል። በወቅቱ አቶ ኦባንግ “ስደተኛ ሆኖ ስደተኛን መሰለል በህግ የተከለከለ ወንጀል ነውና በዚህ ጉዳይ ርህራሄ ሊኖር አይችልም” ነበር ያሉት።
ማርች 11 ቀን በኖርዌይ የኢትዮጵያ ስደተኞች ማህበር አስተባባሪነት ሰላማዊ ሰልፍ ተካሂዶ ነበር። በሰላማዊ ሰልፉ ላይ የፓርላማ ተወካይ፣ የኖአስና/NOASና ዘረኝነትን የሚቃወመው ድርጅት መሪ ተገኝተው ነበር። በሰላማዊ ሰልፉ ተገኝተው ንግግር ካደረጉት መካከል ወ/ት የሺሃረግ በቀለ ይጠቀሳሉ። በኖርዌይ የኢትዮጵያ ስደተኞች ማህበር ጸሐፊ ወ/ት የሺሃረግ በቀለ “እነሱ አገር ቤትም አገር አላቸው፤ በስደትም አገር አላቸው” በማለት ነበር ለ ጎልጉል አስተያየታቸውን መስጠት የጀመሩት።
በሰልፉ ላይ ካቀረቡት ንግግር በተጨማሪ ለጎልጉል አስተያየታቸውን የሰጡት ጸሐፊዋ፣ ስደተኞች ሁሉ አንድ አይደሉም። “ሆን ተብሎ የስደት መረጃና ማስረጃ ማመልከቻው ተመቻችቶላቸው የሚላኩ የወያኔ ቅጥረኛ ሰላዮች አሉ። እነሱ ባለሁለት አገር ናቸው። እኛ አንድም አገር የለንም” ብለዋል። ይህንን ጉዳይ አቅም በፈቀደ ሁሉ ማህበሩ ከአባላቱና ድጋፍ ከሚሰጡት ሁሉ ጋር በመሆን ከዳር እንደሚያደርሰው ገልጸዋል።
“ልብ እንበል” በማለት አስረግጠው የገለጹት ስለ ሁለተኞቹ ስደተኞች ነው። ስርዓቱ ባለው የግፈኛነት፣ የዘረኛነት፣ የከፋፋይነት፣ የዴሞክራሲና የነጻነት እጦት የገፋቸው እውነተኛ ስደተኞች ባግባቡ መልስ ያለማግኘታቸው ጉዳይ ነው። “እነዚህ እውነተኛ ስደተኞች እኔን ጨምሮ አገር የለንም” ሲሉ አገር አልባ የመሆንን ስሜት ይገልጻሉ። ወ/ት የሺሃረግ የኖርዌይ ሚዲያዎችና በስለላ ተግባር የተሰማሩ “ስደተኞች” እንዳሉ በይፋ ቢናገሩም መንግሥት መልስ አለመስጠቱ ቢያሳዝናቸውም ማህበራቸው ትግሉን ይበልጥ እንዲገፋበት እንዳደረገው ነው የሚናገሩት።
ጎልጉል
ኢህአዴግን ሸሽተው አገር ለቀው የተሰደዱ በስደት ምድርም ኢህአዴግ እየተፈታተናቸው እንደሆነ መግለጽ ከሰነበቱ ቆይቷል። በአሜሪካ፣ በካናዳ፣ በጀርመን፣ በስዊድንና በእንግሊዝ አገር ስደተኞችን በመሰለል ተግባር ላይ የተሰማሩ “የስደተኛ ሰላዮች” በስፋት ስለመኖራቸው መረጃ ማቅረብ እንደሚችሉ የሚገልጹ ጥቂት አይደሉም። የተለያዩ ድርጅቶች በዚህ ጉዳይ ምን ያህል እንደገፉበት መረጃ ባይወጣም አቶ ኦባንግ ሜቶ የሚመሩት የአዲሲቷ ኢትዮጵያ የጋራ ንቅናቄ ስራውን ያገባቸዋል ከሚላቸው ክፍሎች ጋር እየሰራ እንደሆነ በዚሁ መድረክ መገለጹ ይታወሳል። በወቅቱ አቶ ኦባንግ “ስደተኛ ሆኖ ስደተኛን መሰለል በህግ የተከለከለ ወንጀል ነውና በዚህ ጉዳይ ርህራሄ ሊኖር አይችልም” ነበር ያሉት።
ማርች 11 ቀን በኖርዌይ የኢትዮጵያ ስደተኞች ማህበር አስተባባሪነት ሰላማዊ ሰልፍ ተካሂዶ ነበር። በሰላማዊ ሰልፉ ላይ የፓርላማ ተወካይ፣ የኖአስና/NOASና ዘረኝነትን የሚቃወመው ድርጅት መሪ ተገኝተው ነበር። በሰላማዊ ሰልፉ ተገኝተው ንግግር ካደረጉት መካከል ወ/ት የሺሃረግ በቀለ ይጠቀሳሉ። በኖርዌይ የኢትዮጵያ ስደተኞች ማህበር ጸሐፊ ወ/ት የሺሃረግ በቀለ “እነሱ አገር ቤትም አገር አላቸው፤ በስደትም አገር አላቸው” በማለት ነበር ለ ጎልጉል አስተያየታቸውን መስጠት የጀመሩት።
በሰልፉ ላይ ካቀረቡት ንግግር በተጨማሪ ለጎልጉል አስተያየታቸውን የሰጡት ጸሐፊዋ፣ ስደተኞች ሁሉ አንድ አይደሉም። “ሆን ተብሎ የስደት መረጃና ማስረጃ ማመልከቻው ተመቻችቶላቸው የሚላኩ የወያኔ ቅጥረኛ ሰላዮች አሉ። እነሱ ባለሁለት አገር ናቸው። እኛ አንድም አገር የለንም” ብለዋል። ይህንን ጉዳይ አቅም በፈቀደ ሁሉ ማህበሩ ከአባላቱና ድጋፍ ከሚሰጡት ሁሉ ጋር በመሆን ከዳር እንደሚያደርሰው ገልጸዋል።
“ልብ እንበል” በማለት አስረግጠው የገለጹት ስለ ሁለተኞቹ ስደተኞች ነው። ስርዓቱ ባለው የግፈኛነት፣ የዘረኛነት፣ የከፋፋይነት፣ የዴሞክራሲና የነጻነት እጦት የገፋቸው እውነተኛ ስደተኞች ባግባቡ መልስ ያለማግኘታቸው ጉዳይ ነው። “እነዚህ እውነተኛ ስደተኞች እኔን ጨምሮ አገር የለንም” ሲሉ አገር አልባ የመሆንን ስሜት ይገልጻሉ። ወ/ት የሺሃረግ የኖርዌይ ሚዲያዎችና በስለላ ተግባር የተሰማሩ “ስደተኞች” እንዳሉ በይፋ ቢናገሩም መንግሥት መልስ አለመስጠቱ ቢያሳዝናቸውም ማህበራቸው ትግሉን ይበልጥ እንዲገፋበት እንዳደረገው ነው የሚናገሩት።
ጎልጉል
Saturday, April 19, 2014
አይ አዜብ! (ዘመናይ ዘ አራት ኪሎ)
አዜብ ሲባል ማን በአዕምሮህ ሊመጣ እንደሚችል እገምታለሁ፡፡ በውስጥህ ያሰብከው ‹የባለራዕዩን መሪ› ባለቤት አዜብ መስፍንን ከሆነ ለጊዜው ግምትህ አልሰራም፡፡ አሁን አዜብ የምልህ ሌላ ሴት ናቸው፡፡ አዜብ አስናቀን ነው፡፡ (አስናቀ ስልህም እንዳትደነግጥ…የሰው ለሰው ድራማው አስናቀ አይደለም፡፡) ለማነኛውም አዜብ አስናቀ የግልገል ጊቤ የኤሌክትሪክ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክት ዋና ስራ አስኪያጅ የነበሩትን ሴት ነው እየጠቀስኩልህ ያለሁት፡፡
እና አዜብን እንዴት አነሳኋቸው ካልክ ጉዳዩ ወዲህ ነው፡፡ ሴትዮዋ ከግቤ ፕሮጀክት ስራ አስኪያጅነታቸው ተነስተው ወደ ሌላ ‹ከፍ› ወዳለ ሹመት መጥተዋል፤ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ኮርፖሬሽን ዋና ስራ አስፈጻሚነት አድገዋል፡ ፡ ሹመታቸው በቀድሞው ስራ አስፈጻሚ አቶ ምህረት ደበበ ቦታ መሆኑ ነው፡፡ እኒህ ሴት ታዲያ ‹አይ› የሚያስብል ነገር ገጥሟቸዋል፤ ወይም እንዲያ እንድንል አድርገውናል፡፡
ሴትዮዋ ይህን ሹመት ካገኙ ወዲህ የት እንዳሉ ጠፍተዋል፤ ማለቴ ከበፊቱ የበለጠ ስልጣን ይዘው ከበፊቱ ያነሰ ነው ወደ ህዝብ በሚዲያ እየወጡ ያሉት፡፡ ታዲያ በእኒህ አዜብ በተባሉ መሐንዲስ ሴት ምክንያት አንዳንድ ‹ጉድ-ዳዮች› እየተሰሙ ነው እልሃለሁ፡፡ ይህ ኢህአዴግ የሚባል ድርጅት ጉዱ ብዙ ነው መቼም! ድርጅቱ የአራት ውላጆች ጥርቅምም አይደል! እና አልኩህ የእኒህ ሴትዮ አባልነት ወይም ወገንተኝነት ከወዴት እንደሆነ ግራ ያጋባል፡፡
አብረን እንጠይቅ እስኪ…እውነት ሴትዮዋ ለማን ይወግናሉ? ለህወሓት ነው? ለኦህዴድ ነው? ለደኢህዴን ነው? ወይስ ኢህአዴግ የሚባለው ራሱን ችሎ ያለ መስሏቸው ተታለው ነው?! በነገርህ ላይ ብአዴን ብዬ ያለጠየኩት በምክንያት ነው፡፡ ምክንያቱ ምን መሰለህ…ሴትዮዋ ብአዴንን እንደማይወግኑ የታወቀ ጥርጣሬ ነው፤ (የታወቀ ጥርጣሬ ምን ማለት ነው አልክ?)
እውነትም ሴትዮዋ ተታልለዋል! እኔን ካልወገንሽ የሚል አተያይ ይገጥመኛል ብለው የሚገመቱ አልመሰሉም ነበር ማለት ነው! ለዚህ ነው ‹መደበቅ› ያበዙት፡፡ ታዲያ አልኩህ ብአዴን ሆዬ ቦታው ለእኔ ይገባኝ ነበር ብሎ ዘራፍ ለማለት ቃጣው አሉ፡፡ በዚህ ምክንያት አለመግባባቱ አይሏልም እየተባለ ነው፡፡ ምክንያት ህወሓት ማንም ዘራፍ እንዲል አለመፈለጉ ነው! በዚህ ምክንያት እኮ ነው አሉ የመብራት መቆራረጡ የባሰበት፡፡ እንዴ ማን ማንን ይምራ!? ፍትጊያቸውን እንጂ ህዝቡን ማን ልብ ብሎት!
አይ አዜብ! ባላሰቡት መልኩ ፍትጊያውን ተቀላቅለው ቁጭ አሉት፡፡ (ከፍትጊያው ከሌሉበት እንኳ በፍትጊያው ምክንያት ስራቸውን እንዳይሰሩ ተደርገዋል!) አንተዬ እነዚህ ኢህአዴጎች ሊበላሉ እኮ ነው፡፡ (ለነገሩ ህዝብን ብቻ እያኘኩ ከሚኖሩ እርስ በእርሳቸውም ቢናከሱ ይሻላቸዋል፡፡ ድሮስ ጅብና ጅብ መቼ ተስማምቶ በልቶ ያወቃልና!)፡፡ የህዝብ አምላክ መልካሙን ቢያመጣ ያምጣ ብሎ ዝም ያለው ህዝብም አንድ ቀን መነሳቱ አይቀርም፡፡ ያኔ ምን ይውጣቸዋል? ካሁኑ እርስ በእርስ ቢበላሉ ከአደባባዩ ገመና ይሻላቸዋል! ለማነኛውም መሐል ሜዳ ላይ የሚዋልሉት አዜብ ጥግ ቢይዙ ሳይሻላቸው አይቀርም፡፡ ምስኪን አዜብ!
http://www.goolgule.com/oh-azeb/
http://www.goolgule.com/oh-azeb/
Friday, April 18, 2014
ይድረስ ለብዙሃኑ የሠራዊቱ አባል ወገናችን!!

ይህንን መረጃ የሰማ ማሰብ የሚችል አዕምሮ ያለው ሰው የሚጠይቀው የመጀመሪያ ጥያቄ “የሠራዊቱ ስብጥር በተገለፀበት ዓይነት የመኮንኖቹም ስብጥር ለምን አልተገለፀም?” የሚል ነው። ይህ ጥያቄ በአስተዋይ ሰው አዕምሮ ውስጥ በተነሳነበት ፍጥነት ምላሽ ያገኛል፤ ምክንያቱም ምላሹ እዚያው እቁጥሮቹ ውስጥ አለ። የመኮንኖቹ ስብጥር ያልተነገረበት ምክንያት አብዛኞቹ መኮንኖች በ17.47 በመቶው በመሆናቸው ነው። ወደዚህ መምደሚያ የሚደርሰው አሳቢው ስለፈለገው ሳይሆን የመረጃው አቀራረብ አመክኖ (ሎጂክ) ወደዚያ ስለሚገፋ ነው። በዚህም ምክንያት በሲራጅ ፈርጌሳ አንባቢነት የቀረበው የህወሓት ሪፓርት በገዛ ራሱ ላይ ነው የተኮሰውም።
እኛ እንደ ሲራጅ ፈርጌሳ የዘር ስታትስቲክስ ውስጥ አንገባም፤ መልዕክታችን ለተገፋውና እየተበደለ ላለው ለመላው የሠራዊቱ አባል ነው።
ይድረስ ሹመትና ኃላፊነት ተነፈገህ፤ የጥቂቶቹን ሀብትና ዝና ጠባቂ እንድትሆን ለተፈረደብህ ወገናችን!!! እስከመቼ ለህወሓትና ጥቂት አጎብዳጅ መኮንኖች ባርነት ትገዛለህ? ይህ ውርደትህ የሚያበቃው መቼ ነው? የታጠቀው መሣሪያ የአገርህና የራስህ ክብር ማስጠበቂያ፤ ነፃነትህን መጎናፀፊያ የምታደርገው መቼ ነው? ለመሆኑ ለመኮንንነት የሚያበቃ ጭንቅላት፣ ልምድ ወይም እውቀት ከፓርቲ አባልነት ነው የሚገኘው? ህወሓቶችና አጋሮቻቸው በሠራዊቱ ያሉትን ቁልፍ ኃላፊነቶችን ሁሉ ጠቅልለው ይዘው “ጀሌዎቻችን እንዲሆኑ ፈቅደንላቸዋል” የሚል ሪፓርት የሚያቀርቡት ምንኛ ቢንቁን ነው? ይህንን ውርደት ኢትዮጵያዊው ወኔህ እንዴት ይቀበለዋል?
ኢትዮጵያዊው ወታደር ከሌላው ኢትዮጵያዊ በባሰ በአምባገነንና ዘረኛ አለቆቹ እየተዋረደ እንደሆነ በገሃድ የሚታይ ጉዳይ ነው። የህወሓት አባላት ቁልፍ የስልጣን ቦታዎችን ይዘው ጦር ሠራዊቱን እንደ ፓርቲ መዋቅር ሲመሩት ማየት የሠራዊቱን አባላት ብቻ ሳይሆን ሁሉንም ኢትዮጵያዊ የሚያንገበግብ ጉዳይ ነው። ሠራዊቱ አገርና ሕዝብን ሊጠብቅበት ይገባ የነገረው መሣሪያ በንጹሃን ዜጎች ላይ እንዲያነሳ፤ ሰላማዊ ሰዎችን እንዲደበድብ፣ እንዲረግጥና እንዲገድል የሚያዙት እነዚህ የህወሓትና ጥቂት አጎብዳጅ አለቆቹ እንደሆኑ የኢትዮጵያ ሕዝብ ያውቃል። ሆኖም የኢትዮጵያ ወታደር የታዘዘው ሁሉ የሚፈጽም ባርያ አይደለምና በእነዚህ ጥቂት ዘረኛ አለቆችህ ላይ እንዲነሳ የኢትዮጵያ ሕዝብ ይጠይቃል።
ውድ የኢትዮጵያ ወታደር ሆይ!!! “ዘረኛነት በቃኝ” በል። ለነፃነት፤ ለእኩልነት፤ ለአገር ክብር በሚታገሉ ወገኖችህ ላይ ክንድህን አታንሳ። የጥቂት ዘረኞችን ሥልጣን በማራዘም ከሚመካብክ የኢትዮጵያ ድሃ ሕዝብ ጋር ዘላቂ ቂም ውስጥ አትግባ። በትእቢት “ሁልሽንም ረግጠን እንገዛለን” ብለው የሚፎክሩት አንተን ከወገንህ ጋር ደም በማቃባት ነውና “እምቢ!” በላቸው። ለዘረኞች ስልጣን ብለህ አትሙት! እንዲያውም ለገዛ ራስህ ክብር፣ ለቤተሰቦችህና ለኢትዮጵያ ሕዝብ ነፃነት ግንባር ቀደም አርበኛ ሁን።
ከላይ የተባለው ለፓሊስ አባላትም ይሠራል። በህወሓትና ህወሓት በየቦታው በፈጠራቸው ጀሌዎች የሚመራ በመሆኑ ከሕዝብ ፍላጎት በተፃፃሪ የቆመ ይምሰል እንጂ የኢትዮጵያ ፓሊስ የሕዝብ ወገን እንደሆነ በተለያዩ አጋጣሚዎች የታየ ጉዳይ ነው። የኢትዮጵያ ሕዝብ በፍትህ እጦት የሚሰቃየውን ያህል ብዙሃኑ ፓሊስ በፍትህ እጦት እየተሰቃየ ነው። የኢትዮጵያ ሕዝብ የኑሮ ጫና እንዳዳከመው ሁሉ የኢትዮጵያ ፓሊስም ኑሮ ከብዶታል። እንደሌላው ሰው ሁሉ ፓሊስንም ዘረኝነት አስመርሮታል። ብዙሃኑ ፓሊስ አቅሙን በጥቂት አምባገነን አለቆቹ ላይ የሚፈትሽበት ጊዜ ደርሷል።
የስለላ ተቋማቱ ጉዳይ ለየት ይላል። “ደህንነት” ተብሎ በሚሞካሸው የጆሮጠቢዎች ስብስብ በሆነው መሥሪያቤት እና በኤክትሮኒክስ ብርበራ የተሠማሩ “ባለሙያ ጆሮ ጠቢዎች” ውስጥ ህወሓት በአለቃነትም በምንዝርነትም አብዛኛውን ቦታ ይዟል። ሆኖም እዚህም የሕዝብ ወገኖች እንዳሉ ይታወቃሉ። በእነዚህ ቦታዎች ያላችሁ የሕዝብ ወገኖች ሲቻል በገሃድ ሳይቻል በሚስጥር ተቋማቱን የማዳከም ሥራችዎችን መሥራት የህሊናና የዜግነት ግዴታችሁ ነው። ከእናንተ ብዙ፤ እጅግ ብዙ ይጠበቃል። የምታሾልኳት ትንሿ መረጃ የብዙዎችን ሕይወት ልትታደግ ትችላለች፡
ግንቦት 7: የፍትህ፣ የነፃነትና የዲሞክራሲ ንቅናቄ በህወሓት የጦር፣ የፓሊስና የስለላ መዋቅሮች ውስጥ የሕዝብ ወገኖች እንዳሉ ያውቃል። እነዚህ ወገኖቻችን እንደሌላው ሕዝብ ሁሉ – አንዳንዴም ከሌላው በባሰ ሁኔታ – በፍትህ እጦት፣ በኑሮ መክበድና በዘረኝነት እየተሰቃዩ መሆናቸው ያውቃል። እነዚህ ወገኖቻችን ጥለው እንዲወጡ፤ ይህ ካልተቻለም ከውስጥ ሆነው የወያኔን የጦር፣ የፓሊስና የስለላ መዋቅሮች እንዲያፈራርሱ ጥሪ ያደርጋል።
ድል ለኢትዮጵያ ሕዝብ!!!
Monday, April 14, 2014
የኢትዮጵያን ወቅታዊ የፖለቲካ ሁኔታ እና የዲያስፖራውን ሚና በተመለከተ በኖርዌይ ኦስሎ ሕዝባዊ ውይይት ተካሄደ
April 14, 2014
የዲሞክራሲያዊ ለውጥ በኢትዮጵያ የድጋፍ ድርጅት ኖርዌይ
በዲምክራሲያዊ ለውጥ በኢትዮጵያ የድጋፍ ድርጅት ኖርዌይ አዘጋጅነት አፕሪል ቅዳሜ 12/2014 በኖርዌይ ኦስሎ ከተማ የኢትዮጵያን ወቅታዊ የፖለቲካ ሁኔታ እና የዲያስፖራውን ተሳትፎ በተመለከተ ታላቅ ሕዝባዊ ስብሰባ ተካሄደ:: በሕዝባዊ ስብሰባው ላይ ቁጥራቸው ወደ ሁለት መቶ የሚጠጉ በኖርዌይ የሚኖሩ ኢትዮጵያኖች ከኦስሎ እና ከተለያየ ከተማ በመምጣት በስብሰባው ላይ የተገኙ ሲሆን የግንቦት 7 የፍትህ የነፃነት እና የዲሞክራሲ ንቅናቄ አመራር አባል አቶ ቡዙነህ ፅጌ የስብሰባው ተጋባዥ እንግዳ በመሆን ሰፋ ያለ ንግግር አድርገዋል::
ሕዝባዊ ስብሠባው በኖሬጅያውያን የሰአተ አቆጣጠር ከቀኑ 15:00 እስከ ምሽቱ 21:00 ሰዓት የተካሄደ ሲሆን የዲሞክራሲያዊ ለለውጥ የድጋፍ ድርጅት ኖርዌይ ሕዝብ ግንኙነት ሀላፊ አቶ አቢ አማረ በኢትዮጵያ ውስጥ በወያኔ አረመናዊ ስርአት በጭካኔ በግፍ ለተገደሉ እና በተለያዩ አስር ቤቶች በፖለቲካ ኣስተሳስባችው ምክንያት ያለወንጀላች የሚስቃዩ ውድ ኢትዮጵያዊን ወገኖቻችን በማስብ በዚሁ ዘረኛ ቡድን አስቃቂ የኣካል ጉዳት ለተፈጸባቸው ኢትዮጵያዊን የአንድ ደቂቃ የህሊና ጸሎት በማስደረግ ስብሰባውን አስጀምረውታል::
በመቀጠለም አቶ ዮሀንስ አለሙ የዴምክራሲያዊ ለውጥ በኢትዮጵያ የድጋፍ ድርጅት ኖርዌይ ሊቀመንበር የመግቢያ ንግግር ያደረጉ ሲሆን በንግግራቸው ስለ ዲምክራሲያዌ ለውጥ የድጋፍ ድርጅት ኖርዌይ አመሰራረት እና ስለ ድጋፍ ድርጅቱ አላማ በማብራራት የድጋፍ ድርጅቱ በአሁኑ ሰአት በሀገር ቤት በሰላማዊ ትግል የወያኔን መንግስት ለመጣል እየታገሉ ያሉትን የፖለቲካ ድርጅቶችን እየረዳ እንደሚገኝ እና ከሀገር ውጭ ደግሞ የወያኔን መንግስት በሁለገብ ትግል ለማስወገድ እየሰራ ያለውን የግንቦት 7 የፍትህ የነፃነት እና የዲሞክራሴ ንቅናቄ የፖለቲካ ድርጅትን በግንባር ቀደምነት እየረዳ እንዳለ በመግለጽ የወያኔን ዘረኛ ስርአት ለመጣል ሁሉም ሰው አስተዋጿ ማድረግ እንደሚጠበቅበት እና ማንኛውም ኢትዮጵያዌ ዜጋ በሀገራችን የጋራ ጉዳይ ስለሆነው የኢትዮጵያ ወቅታዊ የፖለቲካ ሁኔታ ሀሳብ በመለዋወጥ ፣በመካከላችን ያሉትን ማንኛውንም የሃሳብ ልዩነቶች ወደ ኋላ በመጣል ፣ በመቻቻል፣ ሀገር እያፈረሰ እና ሕዝብ እያዋረደ ያለውን የዘረኛውን የወያኔን መንግስት ሁሉም ኢትዮጵያዊ በሁለገብ ትግል ለማስወገድ መረባረብ እንዳለበት አጽኖት ሰጥተው ንግግር አድርገዋል::
በመቀጠለም ዲምክራሲያዊ ለውጥ የድጋፍ ድርጅት ኖርዌይ ድጋፍ ከሚሰጣቸው ድርጅቶች መካከል አንዱ የግንቦት 7 የፍትህ የነፃነት እና የዲሞክራሲ ንቅናቄ አመራር አባል የሆኑት አቶ ቡዙነህ ፅጌ የስብሰባው ተጋባዥ እንግዳ ሰፊውን ጊዜ በመውሰድ ከንጉሱ ስርአት ጀምሮ በደርግ መንግስት ዘመንም በሀገራችን የተደረጉ የፖለቲካ ንቅናቄዎችንና ለውጦችን አንድ በአንድ በመዘርዘር አሁን ካለው የወያኔ ኢህአዲግ መንግስት ጋር በማነጻጸር ሰፋ ያለ ትንታኔ ያቀረቡ ሲሆን አሁን ላይ ሀገሪቱን እየመራው ነው የሚለው የወያኔ መንግስት ከዚህ ቀድሞ ኢትዮጵያን ከመሩት ከሁለቱ መንግስታቶች ማለትም ከንጉሱም ከደርግም መንግስት ጋር ሲነጻጸር ፈጽሞ እንደማይገናኝ የወያኔ መንግስት ዘረኛና የዘረኝነት ፖለቲካ እያራመደ ያለ አረመናዊ መንግስት እንደሆነ አብራርተዋል::
የግንቦት 7 የፍትህ የነፃነት እና የዲሞክራሲ ንቅናቄ አመራር አባል አቶ ቡዙነህ ፅጌ አክለውም ከወያኔ በፊት የነበሩ ሁለቱ መንግስታቶች ለውድቀት የዳረጓቸውን ምክንያቶች በመጥቀስ የወያኔን አንባ ገነናዊ መንግስት ለአፋጣኝ ውድቀት ሊዳርጉት ይችላሉ የሚሉትን ግልጽ ምክንያቶች በመዘርዘር አስቀምጠዋል:: አቶ ቡዙነህ በሁለት የኢትዮጵያ ወቅታዊ ጉዳዮች ላይ በማንሳት እና በማብራራ ከሕዝብ ውይይት እንዲያደርጉበት ለመወያያ ያቀረቡ ሲሆን እነዚህም:
1, በሙስሊሙ ማህበረሰብ እና በወያኔ መካከል ያለው ግጭት
2, የህዳሴ ግድብን በማስመልከት ያለው ተቃውሞ
ስለሙስሊሙ ማህበረሰብ ተቃውሞ ሲናገሩ የሙስሊሙ ትግል በሁለት አመታት ውስጥ የተደረገው ሰላማዊ ትግል በጣም የተሳካና ወያኔ በቀላሉ ሊያዳፍነው ያልቻለው ሰላማዊ መብትን የመጠየቅ ትግል እንደሚያደንቁ በመናገር ነገር ይህ በሙስሊም ማህበረሰብ በኩል እየተደረገ ያለው ትግል እስከ አሁን ድረስ ከመንግስት በኩል ምንም አይነት መልስ ሊያገኝ እንዳልቻለ እና ወደፊትም ከወያኔ መንግስት በኩል ምንም አይነት መልስ ያገኛል የሚል እምነት እንደሌላቸው ተናግረዋል:: ለዚህም ማስረጃው የኢትዮጵያ ሙስሊሞች ከጠየቋቸው አራት የመብት ጥያቄዎች አንዱም ካለመመለሱ በተጨማሪ እስካሁን መሪዎቻቸውም በሃሰት ውንጀላ በእስር እየማቀቁ ያለፍርድ እየተንገላቱ መሆናቸው ነው::
ነገር ገን አሁን እየሆነው ባለው ሁኔታ በእንደዚህ አይነት መንገድ እስከመቼ ድረስ የሙስሌሙ ትግል ይቀጥላል በማለት የተናገሩ ሲሆን አሁን እየሄደ ባለው አካሄድ የሙስሊሙ ተቃውሞ የትግል አቅጣጫውን እስካልቀየረ ድረስ ረጅም ርቀትን ትግሉ ሊቀጥል ይችላል የሚል እምነት እንደሌላቸው እና ነግር ግን የሙስሊሙ ጥያቄ ከእምነት መብት ጥያቄ ባሻገር ወደ የዜግነትን መብት ወደ ማስከበር መለወጥና መሸጋገር እናደለበት በመናገር የሙስሊሙ ማእበረሰብ ጥያቄ ፍሬ ሊያፈራ የሚችለው ትግሉ በዚህ መልኩ ሲቀጥል እንደሆነ ሰፋ ያለ ማብራሪያ ሰተዋል::
በሁለተኛም የህዳሴ ግድብ በሚመለከት ያቀረቡት ሀሳብ ወያኔ የራሱን የፖለቲካ ኪሳራና በህዝቡ ላይ እያደረሰ ያለዉን ግፍ በዕድገት ስም ለመሸፈን ያመጣዉ እንጂ ታቅዶበትና ለህዝቡ በማሰብ እንዳልሆነ በኢትዮጵያና በህዝቡ ላይ እያደረሰ ያለዉ ግፍ እንደ ማስረጃነት በማቅረብ ያብራሩ ሲሆን እንደ ምሳሌም ወያኔ ሃገራዊ የሆነ አላማ ይዞ ካለመነሳቱ አንፃር የሃገርን ድንበር አሳልፎ እስከመስጠት እየሄደ ያለበትን ሁኔታ ጠቅሰው ይህ አሰራር ደግሞ የዲክታተሮች ባህሪ እንደሆነ አብራርተዋል::
የወያኔ መንግስት በህዳሴ ግድብ ሰበብ ምክንያት በማድረግ በመላው አለም ኢትዮጵያኖች በሚኖሩበት ሀገሮች በመዞር የዲያስፖራውን ቀልብ ለመውሰድ የሚያደርገው የአባይ ቦንድ ሽያጭ ሩጫ በዲያስፖራ ተቃዋሚዎች አማካኝነት በፍጹም እንዳልተሳካለት ይህንንም የወያኔ በአባይ ቦንድ ሽያጭ ስም ገንዘብ ዘረፋ በመቃወም ወያኔን አሳፍረው ከመለሱት መካከል በኖርዌይ የሚኖሩ ኢትዮጵያኖች እንደሆኑ በማስታወስ የዚህ የህዳሴ ግድብ ግንባታ ሰበብ የወያኔን መንግስት ወደ መጥፎ ውድቀት ላይ ሊጥለው እንደሚችል በማመን የወያኔ መንግስት በአሁን ሰአት ከግብጽ መንግስት ጋር እየገባ ያለው ሰጣ ገባ ለኢትዮጵያ መጥፎ ሊሆን እንደሚችል በመግለጽ ንግግራቸውን አጠቃለዋል::
በመቀጠልም አቶ ብዙነህ ባነሷቸው ነጥቦችና እና በሌሎችም ጉዳዮች ላይ ከስብሰባው ተሳታፊዎች ለቀረበላቸው በርካታ ጥያቄዎች ማብራሪያ የሰጡ ሲሆን ሰፋ ያለ ውይይትም ተደርጓል፥፥ ከውይይቱም በማስቀጠል የዲምክራሲያዊ ለውጥ በኢትዮጵያ የድጋፍ ድርጅት ኖርዌይ ምክትል ሊቀመንበር አቶ ዳንሄል አበበ የዲምክራሲያዌ ለውጥ በኢትዮጵያ የድጋፍ ድርጅት ኖርዌይ የአቋም መግለጫ ንግግር ያደረጉ ሲሆን ድርጅታቸው ወያኔ በኢትዮጵያ ሕዝብ ላይ እያደረሰ ያለውን ግፍና በደል ፈጽመው እንደሚያወግዙ እና ዴምክራሲያዌ ለለውጥ የድጋፍ ድርጅት ኖርዌይ ሁል ጊዜ ከግንቦት 7 የፍትህ የነፃነት እና የዲሞክራሴ ንቅናቄ ጎን እንደሚቆም ቃል በመግባት የአቶ ቡዙነህ ፅጌን በኖርዌይ በመገኛት ለህዝቡ ለሰጡት ገለጻ አመስግነዋል::
በዝግጅቱ መጀመሪያና ማጠቃለያ ላይ የግንቦት 7 ህዝባዊ ሃይል መዝሙር በመዘምራን የተዘመረ ሲሆን በየጣልቃው የተለያዩ የባህል ዘፈኖች በተወዛዋዦች ታጅቦ የቀረበ ሲሆን ጣእም ያለው ባህላዊ ምግብም በዲሞክራሲያዊ ለውጥ በኢትዮጵያ የድጋፍ ድርጅት ኖርዌይ የሴቶች ክፍል ተስተናግዷል፥፥ ስብሰባውን ተጀምሮ እስኪያልቅ አቶ ፍቅሬ አሰፋ መርተውታል::
በመጨረሻም የዲሞክራሲያዊ ለውጥ በኢትዮጵያ የድጋፍ ድርጅት ኖርዌይ ለዝግጅቱ መሳካት የበኩላችሁን ላበረከታችሁና ከተለያዩ የኖርዌይ ከተሞች ረዥም ርቀት በመጓዝ የዝግጅቱ ታዳሚ ለነበራችሁ ውድ ኢትዮጵያውያን እና እንዲሁም የድርጅቱ አባላቶች ታላቅ ምስጋና እናቀርባለን::
ድል ለኢትዮጵያ ህዝብ !
የዲሞክራሲያዊ ለውጥ በኢትዮጵያ የድጋፍ ድርጅት ኖርዌይ
የመምህራን ፍዳ
(በላይ ማናዬ)

‹‹እኔ ጆርጅ ቡሽን (ፕሬዚዳንት) አላደንቅም፤ ጠፈር ላይ የወጡትንም አላደንቅም፡፡ የማደንቀው እነዚህን ሰዎች ለትልቅ ደረጃ ያደረሷቸው መምህራንን ነው፡፡››
መምህራን የሀገር ምሰሶዎች… መምህርነት የሙያዎች አባት… መምህር የእውቀት ብርሃን…ይህ እውነት ነው፡፡ እውነቱ ግን ዛሬ ላይ ተጋርዷል፡፡ መምህርነትም ሆነ መምህራን የነበራቸው ክብር ዛሬ ላይ በኢትዮጵያ መሬት በአስደንጋጭ ፍጥነት እየወረደ ይገኛል፡፡ መምህራን በሙያቸው እያፈሩ ነው፡፡ እውቀታቸውን እየሰሰቱ ነው፡፡ አዎ፣ መምህራን ጫንቃቸው ጎብጦ ነገን በደበዘዘ ተስፋ የሚጠባበቁ ‹ምስኪኖች› እየሆኑ ነው፡፡ ግን እንዴት?
ካድሬነት Vs መምህርነት
ወጣት ነው፤ ገና ለስራው ዓለም ብዙ አበርክቶት የሚጠበቅበት፡፡ ወጣቱ በአዲስ አበባ አብዮት ቅርስ መሰናዶ ት/ቤ የኬሚስትሪ መምህር ነው፡፡ በስራው ዓለም ለአራት ዓመታት ያህል ቆይቷል፡፡ በእነዚህ ዓመታት ግን የሚሽተው ሙያዊ ተግባሩን ለመወጣት ከብዶታል፡ ፡ መምህርነቱን የሚፈታተኑ በርካታ ጉዳዮች እየተፈራረቁበት ተቸግሯል፡ ፡ ወጣቱ ትዳር መሥርቶ፣ ወልዶና ከብዶ መኖር ቀርቶ ጥሩ ጫማና ልብስ ገዝቶና ጥሩ ምግብ ተመግቦ ለመኖር እንኳ እንዳቃተው ይናገራል፡ ፡ ከተማሪዎቹ በታች እየሆነ የሚታይበትን የኑሮ ጫና መቋቋም እንደተሳነውም ይገልጻል፡፡ በዚህ ሁኔታም ሆኖ ማስተማር ይፈልግ ነበር፡፡ ዳሩ ግን መምህርነቱ ከዚህም በላይ ፈተና አሳይቶታል፡፡ ነጻነቱን ነፍጎታል፡፡
የፖለቲካ ሰዎች (ካድሬዎች) የሚያስተምርበት ድረስ እየሄዱ ተጽዕኖ ያደርጉበታል፡፡ ት/ቤቶች የእውቀት ማበልፀጊያና መጋሪያ ደጆች ቢሆኑም አሁን አሁን ስልጣን ፈላጊዎች መናሃሪያ አድርገዋቸዋል፤ የፖለቲካ ማዕከላት ሆነዋል፡፡
ወጣቱ መምህር ይናገራል፤ ‹‹… የኢህአዴግ ካድሬ ካልሆንክ ችግር ነው፡፡ ካድሬነት ወደህ የምትገባበት ሳይሆን ካድሬ ባለመሆንህ ከሚደርስብህ አድሎአዊ አሰራር ለማምለጥ ብለህ የምትገባበት ሲኦል ሆኗል፡፡ መምህርነት መሰረቱ እውቀት ነው፡፡ አሁን ግን ያ አይደለም መሰረቱ፤ ካድሬነት ነው፡፡ በእውቀት ላይ ብቻ ተመስርቼ አስተምራለሁ ካልክ በድህነት እያከክ ትኖራታለህ፡፡ አንድ ተራ ካድሬ ከአንተ በላይ ገንዘብ ይከፈለዋል፡፡ እናም ብታምንበትም ባታምንበትም ካድሬ ሆነህ ወደ ቀበሌ ከተሾምክ ደመወዝህ 4000 ብር ይደርሳል፡፡ መምህርነት ላይ ከቆየህ ግን ይህን ደመወዝ በ20 ዓመት እንኳ አትደርስበትም፡፡››
እንደ ወጣቱ ገለጻ መምህራን ሙያቸውን አሻሽለው ነገን በተስፋ ለማለም አልታደሉም፡፡ በሙያቸው ክብርን አያገኙም፡፡ ወርን ጠብቃ ከምትመጣ መናኛ ደመወዝ በቀር ሌላ ማበረታቻ ጥቅማጥቅሞች የላቸውም፡ ፡ በእርንቅርት ላይ ጆሮ ደግፍ እንዲሉ ደግሞ መምህራን ከተማሪዎቻቸው ሳይቀር የሚደርስባቸው ንቀትና ማንጓጠጥ እየጨመረ ይገኛል፡ ፡ ‹‹የሚገርምህ አንዳንድ ተማሪዎች ከመምህራን በላይ ስልጣን አላቸው፡፡ ያዝዙሃል ማለት ይቻላል፡፡ ምክንያቱም ካድሬ ተማሪዎች በዝተዋል፤ የተማሪ ደህንነቶችም አሉ፡፡ ስለምታስተምረው ነገር ነጻነት የለህም፡፡ ይህ መምህራንና ተማሪዎች እርስ በእርስ እንዳይግባቡ እየተገነባ ያለ የበርሊን ግንብ ነው፡፡
‹‹ተማሪ መምህሩን እየደበደበ እንዴት ማስተማር ትችላለህ…ለምሳሌ በቅርብ ጊዜ በተማሪ ድብደባ የደረሰበት አንድ መምህር ኮማ ውስጥ ይገኛል፡ ፡ የተማሪ ወላጆችም እኛ መምህራንን እንደ ተላላኪ ነው የሚያዩን፡፡ ምን ታደርጋለህ…አንዱ ልጅ አንዱ የእንጀራ ልጅ የሆነበት ስርዓት ለዚህ አበቃን፡፡ እንደ ባለሙያ ሳይሆን እንደ ሎሌ ነው እየታየን ያለነው፡፡››
ሌላው ያነጋገርኩት መምህር በእንጦጦ አንባ ት/ቤት ታሪክ ያስተምራል፡፡ መምህሩ ቀደም ብሎ የተጠቀሰውን የባልደረባውን አባባል ይጋራል፡፡ ት/ቤቶች የፖለቲካ ማዕከላት እየሆኑ መምጣታቸውንም ይጠቅሳል፡፡ ‹‹…የኢህአዴግ መሰረታዊ ድርጅት የሚባሉ የአደረጃጀት አባላት ት/ቤት ውስጥ ይገኛሉ፡፡ ስብሰባ የሚያደርጉት ት/ቤት ውስጥ ነው፡፡ ለድርጅት ስብሰባ ተብሎ የትምህርት ጊዜ ይባክናል፤ የት/ቤት ንብረት ለፖለቲካ እንቅስቃሴዎች ይውላል፡ ፡ የተማሪ አደረጃጀት የሚባል ነገርም አለ፡፡ በትምህርት ሽፋን የፖለቲካ ስራ የሚሰሩባቸው ናቸው፡፡››
እንደ መምህሩ አባባል፣ መምህራን ሁለት ሚዛን ላይ ሆነው ነው የሚመዘኑት፡፡ የኢህአዴግ አባል የሆኑት በአንድ ወገን፣ አባል ያልሆኑት በሌላ ወገን፡፡ በዚህም አባል ያልሆኑ መምህራን ከሌላው የበለጠ አስተዳደራዊ በደል ይደርስባቸዋል፡ ፡ በፖለቲካ አመለካከታቸው ብቻ እየተለኩ ጫና ይደረግባቸዋል፡፡ ‹‹አንድ ለአምስት የሚባል አደረጃጀት አለ፡፡ መምህራንን በአመለካከታቸው ልዩነት ‹ታርጌት› ይደረጉበታል፡፡ ይህ አንድ ለአምስት የሚባለው አደረጃጀት የፖለቲካ ስራውን ለመከወን የተዘየደ መረብ ነው፡፡ አንዱ አንዱን እየሰለለ እርስ በእርሱ መተማመንን እንዳያጎለብት ነው እንዲህ የተደረገው፡ ፡ በእውነት ት/ቤቶች ዋና የፖለቲካ ማዕከላት እንደሆኑ ደግሜ ደጋግሜ ልነግርህ እችላለሁ፡፡››
የደመወዝ ማነስ፣ መገለልና ንቀት
ደመወዝና መምህራን አልተገናኙም፡፡ ጭማሪ ተደረገላቸው ሲባልም የይስሙላህ ይሆናል፡፡ ለአብነትም 2004 ዓ.ም ላይ መንግስት ለመምህራን የደመወዝ ጭማሪ አደረኩ ብሎ የጨመረውን መጠን ማስታወስ ይቻላል፡፡ የዛኔው የደመወዝ ጭማሪ የመምህራንን ሕይወት የሚለውጥና የሚያሻሽል ሳይሆን ክብረ ነክ እንደነበር ይታወሳል፡፡ እናም የተደረገው ጭማሪ ለመምህራን የማይመጥን እንደነበር በመግለጽ ተቃውሟቸውን ያሰሙ መምህራን (በተለይ በአዲስ አበባ) እንደነበሩ የሚዘነጋ አይደለም፡፡ ከመንግስት የተሰጣቸው ምላሽ ግን ህገ-ወጥ ተብለው ከስራ መሰናበት ነበር፡፡
የመምህራኑ ጥያቄ ግን ተገቢነት ነበረው፡፡ የኑሮ ውድነቱ እየጦዘ ባለበት ወቅት የሰባ ሦስት ብር ጭማሪን ከቁምነገር ቆጥሮ ‹ጭማሪ ተደረገላቸው፤ ጭማሪውም ህይወታቸውን ይለውጣል› እያሉ መልፈፍ በመምህራን ሞራል ላይ ክፉኛ መዘባበት ነበር፡፡ መምህራንም ይህን ሐቅ ይዘው የስራ ማቆም አድማ ሳይቀር አድርገው ነበር፤ ሰሚ አላገኙም፡፡

የገቢ ልክ ማነስ መምህራን በማህበረሰቡ ዘንድ ያላቸውን ቦታ ዝቅ እንዲል እንዳደረገ መምህራን ይናገራሉ፡፡ ‹‹እንደድሮው ሳይሆን አሁን ላይ መምህራን በማህበረሰቡ ዘንድ እጅግ ዝቅተኛ ተቀባይነት ነው ያለን፡፡ መምህር በምንም ሁኔታ ከተማሪው ተሽሎ መታየት አልቻለም፡፡ እስኪ አሁን ከተማሪና ከአስተማሪ የትኛው ነው ላፕቶፕ በእጁ የሚገኘው…ተማሪው ነው፡፡ መምህራን ላፕቶፕ እንኳ መግዛት ይከብዳቸዋል፤ ሳያስፈልጋቸው ቀርቶ ግን አልነበረም የማይገዙት፡፡››
እንደመምህራኑ ከሆነ ማህበረሰቡ ለመምህራን ቦታ አጥቷል፡፡ ‹‹መምህር የተናቀበት ማህበረሰብ ፈጥረናል፡፡ ወዴት እያመራን እንደሆነ አይገባኝም፡፡ ያለመምህር አንዲት ሀገር ወዴትም ልትደርስ አትችልም፡፡›› በእርግጥም መምህራን ቀደም ባለው ጊዜ የነበራቸው ክብር ከፍተኛ ነበር፡፡ እንዲያውም፡-
የእኛ ሙሽራ ኩሪ ኩሪ
አገባሽ አስተማሪ፤ ወሰደሽ አስተማሪ፤
ይባል ነበር፡፡ ‹‹…ዛሬ ላይማ ገና መምህር መሆንህ ሲታወቅ ሰው ይሸሽሃል፡፡ ተስፋ አስቆራጭ ሁኔታ ውስጥ ነው ያለነው፡፡ ለምሳሌ ተማሪዎች ሁሌም መምህሩን እያዩ ተስፋ ይቆርጣሉ፡፡ መማርን ሲያስቡ የተማረውስ የት ደረሰ ብለው ይጠይቃሉ፤ የመምህሩን ህይወት በአጠገባቸው ያያሉ፡፡ ብዙ ተማሪዎች ወደ አረብ ሀገራት ለመሄድና መንጃ ፍቃድ ለማውጣት የሚያስችላቸውን ደረጃ ነው የሚያልሙት፡፡ ተስፋ አይታይባቸውም፡፡ ለምን አትምሩም የሚል መምህር ካለም አንተ የት ደረስክ ብለው ነው የሚጠይቁት፡፡›› ይላል የእንጦጦ አምባ መምህሩ፡፡
የአብዮት ቅርስ ወጣት መምህሩ በበኩሉ፣ ‹‹መምህራን የምንኖረው በኩሽና ቤትና በሽንት ቤት ውስጥ ነው ማለት እችላለሁ፡፡ ጥራት ሳይሆን ዋጋ የሚቀንስ ቤት ነው የምንፈልገው፡ ፡ ገንዘብ የለማ! ይህን ህይወታችንን ደግሞ ተማሪዎች ያያሉ፡፡ ምክንያቱም መምህሩ የሚኖረው በተማሪ ወላጆች ቤት ተካራይቶ ነው፡፡ የወረደ የሚባል ኑሮ ሲኖር እያዩ እንዴት መምህሩን ማክበር ይቻላቸዋል?›› ሲል ይጠይቃል፡፡
ይህ ሁሉ በመምህራን ላይ ለምን?
ያነጋገርኳቸው መምህራን መንግስት ሆን ብሎ መምህራንን የማዳከም ስራ እየሰራ እንደሆነ ያምናሉ፡፡ አንድ ፀሐይ ጮራ ት/ ቤት የሚያስተምር የእንግሊዝኛ ቋንቋ መምህር እንዲህ ሲል ይገልጻል፤ ‹‹የመንግስት ዓላማ መምህራንን ከማንኛውም ለውጥ ለማግለል ነው፡፡ በቀደመው ጊዜ መምህራን ግንባር ቀደም የለውጥ ጠንሳሾችና አንቀሳቃሾች ነበሩ፡፡ በራሳቸው መብታቸውን ያስከበሩና ለሐገርም አለኝታ ነበሩ፡፡ ይህም የሆነው መምህራን በራሳቸው የቆሙ ስለነበሩ ነው፤ በገቢም በእውቀትም ጥሩ ደረጃ ላይ ይገኙ ስለነበር ነው፡ ፡ ስለሆነም ማንኛውንም አይነት ጥያቄ ማንሳት ይችሉ ነበር፡፡ አሁን ግን ስለዕለታዊ ዳቦህ ብቻ እንድታስብ ነው የተፈለገው፡፡ የመብት ጥያቄ ለማንሳት እንዳይቻለን አድርገው ነው የያዙን፡፡››
በእርግጥም አብዛኛውን ጊዜ በማንኛቸውም የለውጥ እንቅስቃሴዎች ውስጥ መምህራን ይኖራሉ፡ ፡ ራሳቸው ነቅተው ማህበረሰቡን በማንቃት የመብትና የዴሞክራሲ ጥያቄዎችን በማንሳት መምህራን ግንባር ቀደሞች ናቸው፡፡ ለአብነትም በኢትዮጵያ አብዮት ወቅት መምህራን ተማሪዎችን በማስተባበርም ሆነ በራሳቸው ተደራጅተው በመንቀሳቀስ ጉልህ ድርሻ ነበራቸው፡፡
ስለዚህም መምህራን አሁንም ለስርዓቱ የማይመቹ ሊሆኑ እንደሚችሉ ኢህአዴግ የተገነዘበ ይመስላል፡፡ ‹‹…ስለዚህ መምህራንን አጥብቆ መያዝ አለበት፡፡ በገቢም በፖለቲካዊ እንቅስቃሴዎችም መምህራን ከእጁ እንዳይወጡ መንግስት ሆን ብሎ የሚሰራ ይመስለኛል፡፡ እንዲያውም አንድ ለአምስት ይህን ለመቆጣጠር የተዘረጋ ነው፡፡ ስለሀገርህ ለውጥ እንዳትወያይ ተራ አጀንዳ በየጊዜው እያወረደ በስራ ይጠምድሃል፡፡ በገቢ እንዳትደረጅ ከልክሎሃል፡፡ ድሮ መኪና ያለው መምህር ነበር፡፡ የራሱ ቤት ነበረው፡ ፡ ሱፍ ለባሽ ነበር፡፡ አሁንስ? አሁን ይህ ሁሉ እንዲኖርህ አይፈለግም፡፡›› ይላል የፀሐይ ጮራ ት/ቤት መምህሩ፡ ፡
የእንጦጦ አምባ መምህሩም ይህን ሐሳብ ይጋራል፡፡ ‹‹…በእርግጥም መንግስት ይህ (መምህራንን ማዳከም) ዓላማዬ ብሎ የያዘው ነገር ባይሆን ኖሮ ህይወታቸውን መቀየር ቀላል ነበር፡፡ ግን አይፈልግም፤ ጥገኛ ሆነው እንዲኖሩ ብቻ ነው የሚፈልገው፡፡ አሁን መምህራን ላይ ቀልድ የማይቀልድ ማን አለ…እንደ መምህራን ደመወዝ ቡን ያድርገኝ የሚሉ ወጣቶች ስንት ናቸው? ይህ ምን ማለት ነው? በራስ እንዳትተማመን ማድረግ አይደለም? ይህ ሆን ተብሎ የተሰራ ስራ ነው፡፡››
ተቆርቋሪ ማጣት!
የኢትዮጵያ መምህራን በ1960ዎቹ መጨረሻና 70ዎቹ ጠንካራ የሙያ ማህበር ነበራቸው፡፡ ያን የመሰለ ጠንካራ መምህራን ማህበር አሁን ላይ ማግኘት እንዳልተቻለ ነው ያነጋገርኳቸው መምህራን የሚገልጹት፡፡ ‹‹ያን ጠንካራ ማህበር አሁን አታገኘውም፤ አፈራርሰውታል፡ ፡ ለምን ያልክ እንደሆን ማሽመድመድ ስለፈለጉ ነው፡፡ ማህበር ለይስሙላ አለ፤ ዳሩ ግን የመምህሩን ጥቅምና ሙያዊ ክብር ማስጠበቅ አልቻለም፡፡ ሲመስለኝ የማህበሩ ዓላማ መንግስትን ማገልገል ነው፡፡
‹‹የሙያ ማህበሩ ተለጣፊ ነው፡ ፡ ለሙያውና ለመምህራን ጥቅም ሳይሆን እንደማፈኛ መሳሪያ የዋለ አድርጌ ነው የማየው፡፡ የሆነ ጊዜ ማህበሩ አይወክለንም ብለን ፊርማ ብናሰባስብ ‹‹የህዝብ ክንፍ ለማፍረስ ተንቀሳቅሳችኋል›› ተብለን ፍዳችን ነው ያየነው፡፡ ይህ የሚያሳይህ ማህበሩ እንደ አንድ የፖለቲካ ክንፍ ሆኖ የሚያገለግል እንጂ ለመምህራን ጥቅም አለመቆሙን ነው፡፡›› ሲል ያብራራል የእንጦጦ አምባ የታሪክ መምህሩ፡፡
እንደ መምህራኑ ገለጻ የሙያ ማህበሩ በየጊዜው መዋጮ ይሰበስባል፡ ፡ ሁሉንም መምህራን በአባልነት እንዳቀፈ አድርጎ ራሱን ይስላል፡ ፡ እውነታው ግን ሌላ ነው፡፡ ‹‹… መምህር ከሆንክ የማህበሩ አባልነት ግዴታ ነው፡፡ ወደድህም ጠላህም ከደመወዝህ ላይ የአባልነት መዋጮ ተብሎ ይቆረጣል፡፡ ከአንድ መምህር በአማካይ 4 ብር ወርሃዊ መዋጮ አለ፡፡ አሁን ባለው መረጃ መሰረት በኢትዮጵያ ያለው የመምህራን ቁጥር ከ350000-400000 ይደርሳል፡ ፡ በአዲስ አበባ ብቻ ወደ 16000 መምህራን አሉ፡፡ ብዙ ገንዘብ እየገባ ግን መምህራን ምንም ሲደረግላቸው አታይም፡፡›› ሲል ይናገራል የአብዮት ቅርስ የኬሚስትሪ መምህሩ፡፡
‹‹ከመምህርነት ማምለጥ››!
እንደ መምህራኑ ገለጻ አሁን ላይ መምህርነት የሚሸሽ ሙያ እየሆነ ነው፡፡ የኬሚስትሪ መምህሩ ይናገራል፤ ‹‹በፊት በፊት መምህር ስትሆን የሞራል እርካታ ይኖርሃል፡ ፡ በማህበረሰቡ ዘንድም ተቀባይነትህ ከፍተኛ ነበር፡፡ ይህም መምህራን ሙያውን እንዲወዱት ያደረገ ነበር፡፡ አሁን ክብር ማጣት አለ፤ ትናቃለህ፡ ፡ መምህር ነኝ ካልክ እንደ አንዳች የሚዘገንን ነገር ፊቱን የሚያዞርብህ ነው የሚበዛው፡፡ እኔ መምህር ነኝ ብዬ አልናገርም፡፡ መምህር ነኝ ስል እንደ መጥፎ ሽታ ሰው የሚያርቀኝ ከሆነ ለምን መምህር ነኝ እላለሁ…? በሙያህ ማፈርን የመሰለ አሳዛኝ ነገር ምን አለ…? ግን እየሆነ ያለው ይህ ነው፡፡››
መምህሩ ከመምህርነት ሙያ መውጣት ይፈልጋለሁ፡፡ ለዚህም ሌላ ዲግሪ እየተማረ ነው፡፡ ‹‹ማምለጥ እፈልጋለሁ፡፡ መምህር ሆኜ መሞት አልፈልግም›› ሲል ተስፋ በቆረጠ ስሜት ይናገራል፡፡ እንደ መምህሩ እምነት መምህራን ሌላ አማራጭ ስራ ቢያገኙ ሁሉም በአንድ ሴኮንድ ት/ቤቶችን ትተው ሊሄዱ ይችላሉ፡ ፡ ‹‹አንዳንዶች ጡረታ ለማስከበር ነው ቀናቸውን የሚጠብቁት፡፡ በዚህ ከቀጠልን ት/ቤቶች ኦና ከመሆን አያመልጡም፡፡››
አሁን ባለው የደመወዝ ስኬል መሰረት አንድ መምህር ከ21 ዓመት በኋላ (በሚገባ እርከኖችን ካለፈ) 3060 ብር ላይ ነው መድረስ የሚችለው፡፡ ለዚያውም ታታሪ የሚባለው መምህር ነው፡፡ ‹‹ታዲያ ተስፋህ ምንድነው? …በግሌ መምህርነት ትልቅ ሙያ መሆኑን አምናለሁ፤ ነውም ደግሞ፡ ፡ ግን አሁን ባለው ነባራዊ ሁኔታ ምክንያት እጠላዋለሁ፡፡ ከማስተማር ሙያ መውጣት አለብኝ፡፡››
የእንጦጦ አምባ ት/ቤት የታሪክ መምህሩም ይህን ሀሳብ ይጋራል፡ ፡ ‹‹እኔ በመምህርነት ዲግሪ አለኝ፡፡ ነገር ግን አሁን ከሙያው መውጣት እፈልጋለሁ፡፡ ለዚህም ወደታች ወርጄ ሌላ ትምህርት በዲፕሎማ እየተማርኩ ነው፡፡ ሙያውን ጠልቸው አይደለም፤ የሚያሰራኝ ሁኔታ ግን የለም፡ ፡ መኖር እኮ አልቻልኩም፡፡ ትዳር መመስረት አልችልም፤ ምን አለኝና ትዳር እመሰርታለሁ፡፡››
•በመጨረሻም የዚህ ጽሑፍ አዘጋጅ ሁለት ነገሮችን ብቻ ማስቀመጥ ይፈልጋል፡፡ አንድ፣ የመምህራንን ጩኸት መንግስት እንዲሰማ ያሳስባል፡ ፡ ሁለት፣ መምህራን ህብረታችሁን አጠናክራችሁ በመታገል ጥቅማችሁን ማስከበር ይቻላችኋልና አድርጉት፡ ፡ ከሙያችሁ መሸሽ ዘላቂ መፍትሄ አይሆንም፤ ስርዓቱ ባይፈልጋችሁም ኢትዮጵያ ትፈልጋችኋለች! ሐገር ያለእናንተ ባዶ ነች፡፡
በመግቢያየ ላይ የጠቀስኩት አባባል የአንድ የባዮሎጅ መምህር የዘወትር ንግግር ነው፤ ታመነ ይባላሉ (ጋሽ ታመነ)፡፡ ይህን ግሩም የጋሽ ታመነ አባባል በድጋሜ ልዋስ፣ ‹‹እኔ ጆርጅ ቡሽን (ፕሬዚዳንት) አላደንቅም፤ ጠፈር ላይ የወጡትንም አላደንቅም፡፡ የማደንቀው እነዚህን ሰዎች ለትልቅ ደረጃ ያደረሷቸው መምህራንን ነው፡፡››
(በቀጣይ፣ ተያያዥ ጉዳዮች ላይ ሌሎች ጽሑፎችን ለማስነበብ እሞክራለሁ፡፡)
ብሩህ ጊዜ ለመምህራን ይሁን! (ምንጭ: ነገረ ኢትዮጵያ)
Wednesday, April 9, 2014
Ethiopia: Telecom Users` Rights Abuse
by Mekonenn Elalla Fekadu
In recent reports by Human Right Watch/HRW/, it emerges how Ethiopia has built up a large monitoring system for controlling citizens network and phone usage. In the country there is telecommunication and network monopoly .And according to HRW there is no constraints that prevent the government from gaining an overview of who have contact with any one on the phones, and internet, in addition, they also save cone phone calls on a large scale. The authorities have an opportunity to store all phone conversations going on the country and outside the country. According to the HRW report ,it often happens in the interrogation that the police are playing phone calls that the arrested person had with family and friends ,specially conversations with someone abroad .This has led many Ethiopians abroad are afraid to call home to Ethiopia.

It is not a secret to any one that the TPLF bandits are doing all they can to remain in powers, so this is one of their tools supposing intimidate all of those who don’t share their evil ideology of hates and especially those denouncing and fighting their tyrant regime. TPLF/EPRDF are specializes on hijacking, assassination, looting and introducing bombs .They are really specialized on the matter of crimes of terrorism. Majority of the people are starving with the lack of foods, and children suffering of malnutrition but the TPLF bandits have means to through millions of dollars to pay for Chines hackers.TPLF hunt for an anonymous blogger who criticized a new law that defies the constitution. The international Telecommunication union/ITU/ estimated internet penetration at 1.5 per cent, this seems surprisingly low, although the precise scale of usage is notoriously difficult to ascertain in Ethiopia. Foryears, the Ethiopia government had systematically restricted access to political content on line.
Bloggers are not immune from legal threats, and a TPLF security wasted valuable time and resources trying to identify an anonymous blogger who had criticized their conflict with a constitutional court. Ethiopia’s telecom sector cannot easily sustain responsible investment .A repressive legal framework that allows for security, privacy, and human rights abuses governs the sector. These laws permits the government to engage in surveillance, censorship, cyber-attacks collect and store user data, and disrupt communications. Although freedom of expression is enshrined in the Ethiopian constitution, the guarantees are qualified by the phrase, cyber-attacks against opposition pages like OLF /Oromo liberation front/and other websites are common in Ethiopia and have intensified following the
protests ,several online forums, websites, and Facebook pages related to the protesters were hacked. It is saddens me to think that, one of the poorest country on earth, deploying the most sophisticated technology to spy its citizens, majority of the people are denied the most simple basic services like clean water,access to reliable telephone services…etc. population of 90 million only 1.5 per cent of the population have an access to internet .I don`t know how on earth one justifies to spend our limited resources frivolously like the way the wanes are spending it. It’s almost a crime for the sake of fake security.
All human beings are born with inalienable rights. These human rights empower people to pursue lives of dignity – thus, no government can bestow them but all governments should protect them. Freedom, built on a foundation of justice, tolerance, dignity, and respect – regardless of ethnicity, religion, political association, or social standing – allows people to pursue these fundamental rights. Whereas dictatorships deny human rights, free societies continually strive to attain them.
Related Posts
Subscribe to:
Posts (Atom)