Sunday, May 12, 2013

ሕወሓት ብኣዴንን እየዋጠው ነው! “ባንድ ወንጭፍ አማራውን በፍጥነት!”



ምንሊክ ሳልሳዊ
ከበረሃው ትግል ጀምረው አብረው እየነጎዱ የመጡት ሕወሓት እና ኢህዴን በኋላም ብኣዴን በአሁኑ ወቅት አጅግ ከባድ የሆነ የፖለቲካ ፊቲጫ ውስጥ መሆናቸውን በዙሪያቸው የሚደረጉት ድርጊቶች እያሳበቁ ነው::በሽግግር መንግስቱ ጊዜ ታምራት ላይኔ ጠቅላይ ሚኒስትር ሆኖ በነበረበት ወቅት በጠቅላይ ሚኒስትሩ ቢሮ ዙሪያ የቀድሞ የኢህኣፓ ሴሎች መሰባሰብን ተከትሎ እንዲሁን ጣምራት የነበረው አቋም ተለክቶ በኤርትራ ጉዳይ ዙሪያ ያለው አመለካከት ተመዝኖ በወያኔ እና በሻእቢያ ጥርስ ውስጥ ገብቶ በሙስና ተፈርጆ በከባዱ አንገቱ እስኪሰብር ቀጥቅውት ከፖለቲካ ጨዋት ውጭ አድርገውታል::Ethiopian police have arrested a minister and 11 other people
እንዲሁም የአዲስ አበባ ከንቲባ የነበረውን ሙሉአለምን በፈንጂ ባህር ዳር ላይ አጥፍተውታል:: የሕወሓት የፖለቲካ ቁማር በዚሁ አላበቃም መለስ ብለን ካየነው ብዙ ነው…..እያለ የቀጠለው የሕወሓት መጦ መትፋት እነ አዲስ ለገሰን እነ ተፈራ ዋልዋን እና ሌሎች የብኣዲን አባላትን ከህዝብ ጋር ከተቀላቀሉ በሁዋላ ኢትዮጵያ ኢትዮጵያ ሸተዋል በሚል መርዛዊ ጥላቻ በጡረታ በጤና ሰንክ በአምባሳደርነት ከአጠገቡ አባሯቸዋል::ለሃገራቸው ይሰራሉ ተብለው የተገመቱ የተጠበቁ የብኣዴን ታጋዮችን ወዴት እንደደረሱ እንኳን ሳይታወቅ አንጠባጥቧቸዋል:: በተጨማሪም በወታደሩ ክፍል የነበሩትን የብኣዴን ጀነራሎች እና የበታች መኮንኖች ለስልጣን ያሰጋሉ በሚል በተለያዩ እስር ቤቶች በመፈንቅለ መንግስት ሙከራ እና በፖለቲካ ስም አስሮ ይገኛል::በቱረታም አባሯል::
ይህን ይህን ያን ያን …እያልን ያለንበት ላይ ስንደርስ ደሞ ከመለስ ዜናዊ ሞት በኋላ በስልጣን ሽኩቻ ዙሪያ የተለያዩ መፋጠጦች እንደነበሩ እንዲሁም እንዳሉ ይታወቃል::ያ መፋጠጥ እና መሿኮት ቀጥሎ በኢህኣዴግ ስብሰባ ላይ በጡዘት ወቶ የነበረ ቢሆንም አልስፈላጊ አደርባይ ሙሰኛ በሚል አደገኛ እንደ ጌታቸው ሴኩትሬ አባባል “የገማ ቂቤ” እየተቀቡ አፋቸውን እንዲይዙ ተደርጓል ብኣዴኖች::
ሕወሓት ለያዘው አላማ እንቅፋት እንደሚሆንበት ከጅምሩ በብኣዴን ላይ የሾሉ ጥርሶቹን እየደጋገመ ሲሞርድ እንደነበር ይታወቃል:; ብኣዴኖች በተለያየ ጊዜያት በሙስና እንዲዘፈቁ እና ማስረጃ እንዲያዝባቸው በአጠገባቸው በሚመደቡ የህወሓት አባላት ከፍተኛ የሆነ ውስወሳ እና ክትትል በማድረግ መዝገባቸውን በሙስና ሰነዶች በመሙላት ለማስወገድ ሚናውን ተጫውቷል:: አሁንም እየተጫወተ ነው:: እንዲሁም ይህንን የፖለቲካ ቁማር በደቡብ ግንባር ላይም እየተጫወተ ይገኛል::
ሕወሓት ነባር የብኣዴን ታጋዮችን ሰብሰቦ ካስወገደ በኋላ በአማራው ክልል የተወለዱ አማርኛ ተናጋሪ ኤርትራውያንን እና የትግራይ ተወላጆችን በመሰግሰግ ጉዞውን ሊቀጥል እየተራወጠ ይገኛል::
ህወሓት በዚህ ሰሞን ደሞ በብኣዴን ባለስልጣናት ላይ ዘመቻ ከፍቷል:: ዘመቻው ሁለት አላማዎችን የያእ ነው እንጂ በፍጹም ሙስና አይደለም::በእርግጥ ሙስና የለም ብለን አንናገርም ሆኖም ሊበሏት ያሰቧትን… እንደሚባለው በፖልርቲካው ላይ ችግር እየፈጠሩ ያሉትን ባለስልጣናት ማስወገድ አስፈላጊ ሆኖ በመገኘቱ ሙስናን እንደቀዳሚ ተደርጎ ለህዝብ ማስነገር አስፈላጊ ነው …ለመሆኑ በሙስና ረገድ ከፍተኛውን የሙስና ባላባቶች የሆኑ የሕወሓት ባለስልጣናት እና የጦር ጄኔራሎች ለምን አይከሰሱም ? አይባረሩም? አይጠየቁም??…ባለፈው ጊዜያት ከጸረ ሙስና ኮሚሽን ዘሎ የወጣ መረጃ እንደጠቆመው የህወሓት አባላት በሙስና መዘፈቃቸውን የሚያሳይ እውነተኛ ምስክር ነው::
ሕወሓት ውስጥ ተንሰራፍቶ የሚገኘው የሙስና ድርጊት እንደት ነው ሊወገድ የሚችለው?? ለምንስ የህወሃት ሙሰኞች ለፍርድ አይቀርቡም ስልጣናቸውንስ አይነጠቁም?? የጦር ጄኔራል የሆኑ የሕወሓት ቅምጥ መኮንኖችስ ለስልታን ጥበቃ በሚል ሰበብ ለምን ዝም ይባላሉ?? ይህን እና ተመሳሳይነት ያላቸው ጥያቄዎች ለመመለስ የሚከብድ ነው ለወያኔ::
በዚህ ሳምንት ደሞ እንደፋሽን የተያዘው ነገር ቢኖር ብኣዴኖችን መግቢያና መውጫ አሳጥቶ አፋቸውን በማስያዝ ምንም አይነት ጥያቄ እንዳይጠይቁ እና አንገታቸውን እንዲሰብሩ ማድረግ ነው::
ትላንት እና ጠዋት የደረሱን ማስረጃዎች እንዳመለከቱን ከሆነ መገናኛ አከባቢ በሚገኘው የጉምሩክ ዋና መስሪያቤት ውስጥ ሲቭል በለበሱ ደህንነቶች እና በፌዴራል ፖሊስ የታጀበ ኦፕሬሽን እየተደረገ እንደሆነ ቢያመለክትም በውስጥ የነበሩ ከ200 በላይ ሰራተኛች የሃገር ጉዳይ ነው ተብለው እንደወጡ እና አቶ መላኩ ብጫውን ታግቶ እንደነበር እና በኋላም በምን እንደሆነ ሳይታወቅ አቶ ገብረዋህድ እና ሌሎች የመምሪያ ሃላፊዎች በቁጥጥር ስር እንደዋሉ ተነግሮ ነበር :; ይህንን ለማጣራት በተደረገ ሙከራ መረጃ የሚሰጡን የብኣዴን እና አንዳንድ የሕወሓት አባላት ስልካቸውን እስከ ማታ ድረስ እንዲዘጉ ታዘው ነበር::
መረጃዎች እንደጠቆሙት በአቶ መላኩ ፈንታ እና በአቶ ገብረዋህድ መካከል ምንም አይነት መግባባት እንደሌለ እና በኣንድነት ሙስና ይፈጽማሉ ሊያስብል የሚችል አንድም ሁኔታ የለም ይላሉ እንደውስጥ አዋቂዎች እምነት:: ገብረዋህድ በጉምሩክ ባለስልጣን ውስጥ ፈላጭ ቆራጭ ሲሆን አቶ መላኩ እንደበላይነታቸው ሙሉ ስልጥኣን አልነበራቸውም:: አቶ መላኩ የፈረሙትን ገብረዋህድ ይሽር እንደነበር እና ይህም ጉዳይ ጥቆማ እስከ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ደርሶ ውሳኔ ደፍሮ የሰጠ አልነበረም::ገብረዋህድ ማለት እጅግ ቀንደኛ ዘረኛ የሆነ ሰው እንደሆነ ይታወቃል ስለዚህ ኢትዮጵያ ከሚለው መላኩ ጋር ተስማምቶ ሙስና ይሰራል ማለት ዘበት ነው::ታማኝነትም የለውም ::ገብረዋህድ ባንድ ወቅት በመስሪያ ቤቱ እነና ስርኣቱ ህልውናችን አንድ ነው ያለ ደፋር እና ዘረኛ ሰው ነው በሙስና ተብሎ ዘብጥያ መውረዱ አጠያያቂ ሲሆን እንደኔ ብኣዴኖችን ለመጥለፍ የተሸረበ ሴራ ነው::
ገብረዋህድ ከወይዘሮ አዘብ ጋር ቀረቤታ እንዳለው ይታማል:: ከላይ እስከ ታች በጉምሩክ ውስጥ የሞሉት የትግራይ ተወላጆች በሙስና ተጨማልቀዋል::እንዲሁም ስርኣቱ እጅግ ከሚንከባከባቸው ሰዎች አንዱ ነው:: በተለያየ ጊዜ የህወሃት ባለስልጣናት እና የጦር ጄኔራሎች በተለያየ ጊዜ ከውጪ የሚያስገቧቸውን ማንኛውም ነገሮች ጉምሩክ በነጻ እንደሚያሳልፍላቸው ሲታወቅ የህ ደሞ የገብረዋህድ ተትእዛዝ እንደነበር መረጃዎች ይጠቁማሉ::
በመከላከያ ሚኒስቴር ውስጥ ጸሃፊ ሆና የምትሰራ አንዲት የመሃል አገር ሰው የሆነች ትግሪኛ ተናጋሪ እንደነገረችኝ በተለያየ ጊዜያት ከጄኔራሎቹ አልፎ እሷ ራሷ ከተለያዩ አገሮች የምታስገባቸው እቃዎች በነጻነት ቤቷ ድረስ ተጭነው እንደሚመጡ አጫውታኛለች::
ይህን ተከቶ አቶ ብርሃነ ሃይሉ እና አቶ ሴኩቱሬ ጌታቸው በአማራነት ከህወሃት ተባረዋል :: ህወሓት ወዴት እያመራች ነው?? አማራውን እያደነዘዘች ማጥፋት :: ይህ ሊታገሉት የሚገባ ጉዳይ ነው:: ምክንያቱም ባለፉት ጊዜያት የተደረጉ ጉዞዎች ያልጣሟቸው ባለስስልታናት ጥያቄ እያቀረቡ ባሉበት በዚህ ወቅት እየተወሰዱ ያሉ እርምጃዎች መመልከት እና ማመዛዘን የራሳችን ድርሻ ነው::

No comments:

Post a Comment