ባህርዳር በተቃዉሞ እየተቀወጠች ነዉ፡፡አዲስ አበባም እንዲሁ!
በባህርዳሩ ተቃውሞ ሰባት ሰዎች ሲቆስሉ ሶስት ሞተዋል፡፡
ዛሬ ጠዋት ባህርዳር ከተማ ላይ የተነሳውን የህዝብ ተቃውሞ ፖሊስ በኃይል ለመበተን ጥረት እያደረ ቢሆንም ህዝቡ በብዛት ተቃውሞውን እየተቀላቀለ መሆኑን ከቦታው የደረሰን መረጃ ያመለክታል፡፡ ፖሊስ በተኮሰው ጥይት ሁለት ወጣቶች ህይወታቸው ያለፈ ሲሆን ሌሎች አምስት ያህል ወጣቶች እንደቆሰሉ ተገልጾአል፡፡
በአሁኑ ወቅት ከቀበሌ 10 አባይ ማዶ ያለው መንገድ ተቃውሞውን በተቀላቀለው ህዝብ የተዘጋ ሲሆን ወደ ጎንደር የሚወስደው መንገድም መዘጋቱ ታውቋል፡፡ የቀበሌ 8፣ 10ና 11 ነዋሪዎች እንዲሁም የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ተማሪዎች ተቃውሞውን እየተቀላቀሉ ነው ተብሏል፡፡ የአፈ ጉባኤ ጽ/ቤት አካባቢም በርካታ ህዝብ የተገኘ ቢሆንም ርዕሰ መስተዳደሩን ጨምሮ ሌሎች ባለስልጣናት የሉም እንደተባሉ ገልጸውልናል፡፡
ይህ በንዲህ እንዳለ በአዲስ አበባ ቤኒ መስጅድ በዛሬዉ ዕለት ሙስሊሙ ማህበረሰብ በረቀቀ መልኩ የተቃዉሞ ጽሁፎችን በፊኛ በማዘጋጀት ጸረ ወያኔ ተቃዉሞ አሰምተወል። መንግስት በሴኩላሪዝም ሽፋን እየፈጸመ ያለውን የሂጃብ ገፈፋ የሚያወግዝና በተጨማሪም በህዝበ ሙስሊሙ መፍትሄ አፈላላጊ ኮሚቴዎች ላይ እጸፈጸመ ያለውን የፍጥ መዛባት፣ በማረሚያ ቤቱ የሚፈጸሙ ግፎችን ለማውገዝ ነው። መንግስት ሙሉ በሙሉ ተቃውሞውን በሃይል አስቁሚያለሁ ሲል የነበረ ቢሆንም ህዝበ ሙስሊሙ ግን ድንገተኛ ተቃውሞ በማድረግ አስገራሚ ተቃውሞውን ገልጽዋል። ከላይ ነዉና ትዛዙ ዘንድሮ ይህ ለክርስቲያኑም ሆነ ለህዝበ ሙስሊሙ የማይበጅ ባንዳ ስርዓት ሞት-ሞት እየሸተተዉ ነዉ።ድል ለጭቁኑ የኢትዮዽያ ህዝብ !!!
No comments:
Post a Comment