Monday, February 3, 2014

ለሌተናል ጄነራል ጃገማ ኬሎ በባለራዕይ ወጣቶች ማህበር የክብር መግለጫ ተበረከተላቸው


February 3, 2014 10:15 am
  • digg
  • 56
     
    Share
የባለራዕይ ወጣቶች ማህበር ትላንት ጥር 25 ቀን 2006 ዓ.ም ለኢትዮጵያ አንድነትና ሉአላዊነት መከበር ያበረከቱትን ከፍተኛ አስተዋፅኦ እውቅና ለመስጠት በቅርቡ 93ኛ ዓመታቸውን ላከበሩት ሌተናል ጀነራል ጃገማ ኬሎ የክብር መግለጫ ምስክር ወረቀት እንዳበረከተላቸው የማህበሩ ምክትል ጸሀፊ ለፍኖተ ነፃነት ገለፁ፡፡1797118_415026495298978_204746632_n


የባለራዕይ ወጣቶች ማህበር ም/ጸሀፊ ወጣት ጥላዬ ታረቀኝ ለፍኖተ ነፃነት የሚከተለውን ብሏል “ሌተናል ጄነራል ጃገማ ኬሎ ሀገራቸው ኢትዮጵያ ታላቅ ተጋድሎ የፈፀሙ ናቸው፤ ማህበራችንም በኢትዮጵያ አንድነት ዙሪያ ስለሚሰራ እንደነዚህ አይነት ጀግኖችን ክብር ይሰጣል፡፡ ለዚህም ነው ለሌተናል ጀረናል ጃገማ የክብር ምስክር ወረቀት የሰጠናቸው፡፡ ”  አያይዞም “የብሔር ግጭቶች እንዳይፈጠሩና  ዜጎች በኢትዮጵያዊነታቸው ላይ እንዲያተኩሩ የድርሻቸውን ተወጥተዋል፡፡” ሲል ለሌተናል ጄነራል ጃገማ ኬሎ  ስለተሰጠው የክብር መግለጫ አብራርቷል፡፡
የባለራዕይ ወጣቶች ማህበር አመራሮችና አባላት ለሌተናል ጄነራል ጃገማ ኬሎ በመኖሪያ ቤት በመገኘት የክብር መግለጫ  ምስክር ወረቀት ሲያበረክቱላቸው የአካላቸውን መድከም ተቋቁመው በሙሉ ወኔ ወጣቱ ትውልድ በዘር መከፋፈሉን ትቶ ኢትዮጵያን እንደቀድሞው አንድ ለማድረግ እንዲታገል መልዕክት ማስተላለፋቸውን ወጣት ጥላዬ ተናግሯል፡፡1624557_415026681965626_2146485222_n
- See more at: http://www.fnotenetsanet.com/?p=6173#sthash.jVnhrWOk.dpuf

No comments:

Post a Comment