Friday, June 26, 2015

ሙታንን የከፋፈለው የህወሓት ‹‹ብሄርተኝነት›› (ጌታቸው ሽፈራው)


June 24, 2015
ጀርመን ውስጥ በነበረበት ወቅት ጠባብ ብሄርተኝነት ምን እንደሆነ በተግባር የተገነዘበው የሳይንሱ ሊቅ አልበርት አንስታይን ጠባብ ብሄርተኝነትን የሰው ልጅ አጥፊ በሽታ ነው ይለዋል፡፡ አውቁ ሳይንቲስት ይህን በሽታ በቀላሉ የማይድን፣ የሰውን መላ ሰውነት የሚያበላሽ እከክ አይነት ወረርሽኝ ጋር ያመስለዋል፡፡ የህወሓት በሽታም ይህ የኑክሊየር ፊዚክስ ቀመሩ ባለቤት የገለጸው ጠባብ ብሄርተኝነት ነው፡፡ ደርግ በትግራይ ጨምሮ በሁሉም የአገራችን ክፍሎች ህዝብ ጨፍጭፏል፡፡ ይህን ጭፍጨፋ በኢትዮጵያውያን ላይ የተደረገ በደል አድርጎ ከመቁጠር ይልቅ በብሄር አይን መንዝሮታል፡፡ እናም ሰኔ 15 ‹‹የትግራይ የሰማዕታት ቀን›› በሚል ለ26ኛ ጊዜ አክብሯል፡፡
እንግዲህ ትግራይ ውስጥ ደርግ የጨፈጨፋቸውን ኢትዮጵያውያን ከሞቱ በኋላም እንደ ኢትዮጵያውያን እንዳናስባቸው በቋንቋ መስመር ታጥረናል ማለት ነው፡፡ በመላው አገሪቱ ጭፍጨፋዎች ነበሩና ሌሎች ከ80 በላይ ‹‹ብሄሮች››ም የየራሳቸውን ሰዕማታት ቀን ሊያከብሩ መሆኑ ነው፡፡ ደርግ አሁን ትግራይ ተብሎ በተከለለው የኢትዮጵያ ክፍል ባደረገው ጭፍጨፋ አፋርኛ፣ አማርኛ፣ ኦሮምኛ….ሌሎችም ቋንቋ ተናጋሪዎች ለገበያ አሊያም በሌላ ምክንያት በአካባቢው በመገኘታቸው የጭፍጨፋው ሰለባ የሆኑት ነፍሳቸው የሰው ነፍስ አይደለም ማለት ነው፡፡
በተመሳሳይ በሌሎች አካባቢዎች በተደረጉ ጭፍጨፋዎች ትግርኛ ተናጋሪ ኢትዮጵያውያን የጭፍጨፋው ሰለባ ሆነዋል፡፡ ሆኖም ህወሓት ሀውዜንም ሆነ ሌሎች አካባቢዎች በተደረጉት ጭፍጨፋዎች ሰለባ የሆኑት ‹‹ትግሬዎች ብቻ ናቸው!›› ብሎ ለብቻው የሙት አመት እያከበረ ነው፡፡ በዚህም ትግራይ ውስጥ በደርግ የተጨፈጨፉ ሌላ ቋንቋ ተናገሪዎች ደመ ከልቦች ሆነዋል፡፡
ህወሓት ማንን ያስቀድማል?
አንድ ሀቀኛ ፓርቲ ከስልጣን ይልቅ ሊያስቀድመው የሚገባው ወክየዋለሁ የሚለውን ህዝብ ነው፡፡ ሆኖም አንዳንድ ፓርቲዎች በስም ወክለነዋል የሚሉትን ህዝብ እንዳስቀደሙ በማስመሰል ቅድሚያ የሚሰጡት ስልጣናቸውን ነው፡፡ ከዚህ ሲከፋ ደግሞ ስልጣናቸው በራሱ ወክየዋለሁ የሚሉትን ህዝብ ከመውደድ ይልቅ ሌላ ህዝብን በመጥላት ላይ ሊመሰረት ይችላል፡፡ አጠቃላይ የአገሪቱን ህዝብ የሚጠሉ ከሆነ ደግሞ የሚወዱት ስልጣንን ብቻ ይሆናል፡፡ የህወሓት ስልጣን የተመሰረተው ሌሎችን በመጥላት ላይ ነው፡፡ ህወሓት የትግራይን ህዝብ ቢወድ ኖሮ በጠባብ ብሄርተኝነት ከሌላው የኢትዮጵያ ህዝብ ለመነጠል ባልጣረ ነበር፡፡ በመላ ኢትዮጵያ የሞቱትን ትግርኛ ተናጋሪዎች ሞት ረስቶ ክልሉ ውስጥ የሞቱትን የሚረሳበት አጋጣሚ አይፈጠርም ነበር፡፡ ለኢትዮጵያ ህዝብ ፍቅር ቢኖረው ደግሞ ትግራይ ውስጥ የተጨፈጨፉትን ኢትዮጵያውያን ከሰው ሳይቆጥር የእኔ ነው ያለውን ህዝብ ብቻ በቋንቋ ለይቶ ባላስታወሰ ነበር፡፡
ህወሓት ይህን ጥላቻን መሰረት ያደረገ ጉዞውን አርበኝነት ይለዋል፡፡ ስሙ እንኳ ይህን ለትግራይ ህዝብ አርነት የቆመ መሆኑን ያስረዳል፡፡ የፈረንሳ ቻረለስ ዲ ጎል ህወሓትን አይነት አካሄድ አርበኝነት ሳይሆን በጥላቻ ላይ የተመሰረተ ጠባብ ብሄርተኝነት አድርጎ ይወስደዋል፡፡ እንደ ቻረለስ ዲ ጎል አርበኝነት ማለት የህዝብን ፍቅር ስታስቀድም የሚመመጣ ነው፡፡ በተቃራኒው ጠባብ ብሄርተኝነት ለራስህ ህዝብ ያለህን ፍቅር በመቅደሙ ሳይሆን ለሌሎች ህዝቦች ያለህን ጥላቻ ስታስቀድም የሚመጣ ክስተት ነው፡፡ ይህ የፈረንሳይ የቀድሞ ፕሬዝዳንት ህወሓትን በስርዓት የገለጸው ይመስለኛል፡፡ በመሆኑም ህወሓት ወክየዋለሁ የሚለውን የትግራይን ህዝብም አይደለም፡፡ ቀሪው የኢትዮጵያ ህዝብ ላይማ ዲ ጎል እንደሚለው ጥላቸው የከረረ ነው፡፡ በዚህ መሃል የቀረው አንድ ነገር ብቻ ነው፡፡ ስልጣን! ከሁሉም አስቀድመዋለሁ የሚለውን የትግራይ ህዝብም የስልጣን መጠቀሚያ ነው፡፡ ‹‹የትግራይ ሰማዕታ ቀን›› ብሎ ሲያውጅም ‹‹የሞትነው እኛ ነን፡፡ በመሆኑም ስልጣን ላይ መቆየት ያለብን እኛ ነን›› ብሎ ለስልጣን ምሽግ መቆፈሩ ነው፡፡
ኦስካር ስትራውስ የተባሉ ሌላ ሰውም እንደ ዲ ጎል ሁሉ ብሄርተኝነት አርበኝነት ሆኖ አያውቅም ይላሉ፡፡ ከብሄርተኝነት በእጅጉ የተሻለና ድንበርና ሌሎች መከለያዎች የማይገድቡት አርበኝነት አለ የሚሉት እኝህ ሰው አርበኝነትን የቋንቋም ሆነ ሌላ ድንበር ሊለየው አይገባም ባይ ናቸው፡፡ ይህ አርበኝነት ድንበር ሳይገድበው የሰው ልጅ ስልጣኔ የሰጠውን ተስፋ የሚያስቀጥለበት ከሆነ ብቻ ነው፡፡ ድንበር የሚገድበው አርበኝነት ከዚህ በተቃራኒ የሰው ልጅን ስልጣኔ የሚያከስም እኩይነት ነው፡፡ አብዛኛዎቹ ምሁራን እንደ ህወሓት ያሉትን የፖለቲካ ሀይሎች ላይ በተመሳሳይ የሚዘምቱ ናቸው፡፡
ለምሳሌ ያህል ቶርሰሪን ቬብለን ጠባብ ብሄርተኝነትን ሞራል ባጣ መንገድ የተወለደ እና ሰይጣናዊ በሆነ መንገድ የሚመለክ መሆኑን ያሰምሩበታል፡፡ አስቀጥለውም ይህ መስረቱ እኩይ የሆነ አስተሳሰስ የሰው ልጅን ተቋማትና አጠቃላይ ኑሮ በአለመግባባትና በጭንቀት ከመወጠር አልቆመመም ሲሉ ኢትዮጵያ ያለችበትን አይነት ሁኔታ ቀድመው የተገነዘቡ ያስመስላቸዋል፡፡
በአገራችን ብሄር ‹‹ከሲቪል›› ተቋማት አልፎ ቤተ እምነት ውስጥ አለመግባባትና አለመተማመን እየፈጠረ ቀጥሏል፡፡ ቀበሌ ብቻ ሳይሆን ቤተ ክርስቲያንና መስጊድ ውስጥም ሳያዩ ያምናሉ በሚባሉት ኢትዮጵያውያን ላይ ‹‹ብሄር›› የልዩነት ምክንያት ሆኗል፡፡ ከአመታት በፊት ጳጳስ ከተቀናቃኞቻቸው ግብጽ ሲመጣ በፍቅር ይቀበሉ የነበሩት ኢትዮጵያውያን አሁን የቤተ ክርስቲያን መሪዎችን በ‹‹ብሄር›› አይን እንዲያዩ ተገድደዋል፡፡ ለዚህ ደግሞ ህወሓት ቀዳሚውን ድርሻ ይወስዳል፡፡ የድርጅቱ የቀድሞ ሊቀመንበር በመጽሃፋቸው እነ ስብሃት ነጋ ደብረ ዳሞን የመሳሰሉ ገዳማት ሳይቀሩ የህወሓትን አባላት አስርገው ሲያስገቡ መቆየታቸውንና በአሁኑ ወቅት በመላው አገሪቱ የሚሰራበት መሆኑን አምነዋል፡፡ ኢትዮጵያውያንም የእምነት፣ የቋንቋና ሌሎችም ሳይወስኗቸው ከሚገናኙባቸው ነገሮች አንዱ ሀዘን ነው፡፡ በዚህ ረገድ ኢትዮጵያውያን የራሳቸውን የሆነን ልዩ ማህበራዊ መሰረትና ተቋማት መስርተዋል፡፡ አሁን ግን ሟች በ‹‹ብሄር›› አጥር ታጥሯል፡፡ ሁሉም ‹‹ሟችህን በየ ቋንቋህ አስብ›› ተብሎ መከለል ተጀምሯል፡፡ ይህ እንግዲህ ቶርሰሪን ቬብለን መሰረቱ አሉታዊ መሆኑን የሚገልጹት ጠባብ ብሄርተኝነት እስከ ለቅሶና ቀብርም ወርዶ የኢትዮጵያውያንን ማህበራዊ ትስስርና ተቋማት ማንኮታኮቱን ነው የምንረዳው፡፡
በአሁኑ ወቅት በርካታ ቀናት የሚከበሩት በአለም አቀፍ ደረጃ ነው፡፡ የሴቶች፣ የሰራተኞች፣ የጋዜጠኞች… ብቻ በርካታ ቀናት የሚታሰቡት በአለም አቀፍ ደረጃ ነው፡፡ ምክንያቱም ዘመኑ በአገር ብቻ የሚታጠርበት ባለመሆኑ ነው፡፡ ኢትዮጵያውያን ጨምሮ በርካታ ህዝቦች በሩዋንዳና በሌሎች አገራት የተፈጸሙን ጭፍጨፋዎች ያወግዛሉ፡፡ ጭፍጨፋን በተመለከተም አለማቀፍ ቀናት ይከበራሉ፡፡ አሁን በአገራችን እየተደረገ ያለው ግን ከአለም አቀፍም ወርዶ በ‹‹ብሄር›› ሆኗል፡፡ ኢትዮጵያውያን ቋንቋውን ካልተናገሩ በስተቀር የተጨፈጨፉ ወንድሞቻቸውን ቀን ለማስብ እንዳይችሉ የ‹‹ብሄር›› አጥር ታጥሮባቸዋል፡፡

I need my dad to be here, pleads daughter of ‘Ethiopian Mandela’ as she stars in play dramatising plight of kidnapped father


Helawit Hailemariam
Helawit Hailemariam, centre, with, from left, Doyin Ajiboye, Justine Onokoko, Nadia Carrier Solomon and Nubia Servina 
Published: 26 June, 2015
by KOOS COUVÉE
IMAGINE celebrating your 16th birthday while your loving dad, who has committed no crime, is on death row 4,000 miles away in a jail where you fear he may be tortured.
This scenario is in fact reality for Helawit “Holly” Hailemariam, 15, from Clerkenwell, whose father, Andargachew Tsege, a British man from Holloway and a prominent opposition activist in his native Ethiopia, is languishing in a jail in the East African country.
On Wednesday, a new play by Islington Community Theatre starring Helawit and five of her friends marked the anniversary of Mr Tsege’s kidnapping while he was travelling through Yemen. 
Her father, also known as Andy, has been kept in secret detention in Ethiopia ever since – the authorities will not even tell his family where he is being held, or allow any contact.
The family hopes the play will pile pressurise on the UK government to press the Ethiopians to release Mr Tsege. It had its first showing at Platform, in Holloway, this week in front of a packed audience, who included his partner and two other children. 
Helawit, who plays herself, is seen living the life of a normal teenage girl while at the same time having to deal with her father’s chilling disappearance. In real life, she has just finished her GCSEs at Elizabeth Garrett Anderson School in Angel. 
The play highlights government inaction over the plight of “the Ethiopian Nelson Mandela”. After the performance, Helawit said: “My dad has been absent for a year and I am going through so many changes and I need him to be here. 
Helawit “Holly” Hailemariam and dad Andargachew Tsege
“We are very worried and we feel the Prime Minister and the government are not doing anything at all.”
She said she was grateful for the way friends had rallied round. “They have really supported me, especially Nadia [Carrier Solomon],” she said. “She knew what I was going through early on.”
The teenager, who will be starting her A-levels at LaSWAP Sixth Form in Parliament Hill in September, said the play may transfer to a south London theatre and be seen at the Edinburgh Festival Fringe.
Mr Tsege, a naturalised British citizen who has lived in London since 1979, is an outspoken critic of the Ethiopian regime and a member of the exiled opposition group Ginbot 7. 
The jazz fan was on his way to an opposition conference in Eritrea when he was kidnapped by the Yemenis and handed over to Ethiopian authorities, who had sentenced him to death in absentia in 2009 for conspiring to commit “terrorist acts”. 
Human rights organisation Reprieve is concerned that he is being held in solitary confinement and has been tortured.
On Wednesday, Foreign Secretary Philip Hammond said he had spoken to Ethiopia’s Foreign Minister and expressed “deep concern” over Mr Tsege’s solitary confinement.
Helawit’s mother, Yemi Hailemariam, 47, who is spearheading a campaign to have her partner released, was tearful after the play. She said: “It makes me so sad. The government is not pushing enough. We have to make them so we can get him back.”
A petition calling for the release of Mr Tsege has been signed by more than 120,000 people.