Friday, August 30, 2013

“ምስጢር ያልሆኑ ምስጢራት” ‑ ድንበር ተሻጋሪው የኢሕአዴግ ዕኩይ ፕሮፖጋንዳ


August 30, 2013
ከኢትዮጵያዊ ሙስሊም
እዚህ አሜሪካ ከዋሽንግተን ዲሲ ከተማ የሚሰራጨው የኢትዮጵያ ዳያስፖራ ራዲዮ ጣቢያ በቅርቡ የሙስሊም ኢትዮጵያውያን የሃይማኖት ነፃነትና መብትን የማስከበር ሰላማዊ ትግልን ከ‹ፖለቲካዊ እስልምና› ጋር ለማያያዝ የሚቃጣ “የራዲዮ ዝግጅት” አቅርቧል፡፡ ዝግጅቱ ዊኪሊክስ በተሰኘው ድረ‑ገፅ አምና ይፋ የተደረጉ የስቴት ዲፓርትመንት ምሥጢራዊ ሰነዶችንና ከጥቂት ዓመታት በፊት በኢትዮጵያ አንዳንድ አካባቢዎች ከተከሰቱ ግጭቶች ጋር የተያያዙ የድምፅ ግብዓቶችን በመጠቀም ወቅታዊውን የኢትዮጵያውያን ሙስሊሞች የሃይማኖት ነፃነትን የማስከበር ሰላማዊ ትግል ከ‹ፖለቲካዊ እስልምና› ጋር በማያያዝ ጭቃ ለመቀባት፣ ብሎም ሙስሊም ያልሆኑ ወገኖችን ግንዛቤ ለማዛባት ይሞክራል፡፡
ይህ ጽሑፍ በአገር ውስጥም ሆነ በውጭ ለሚገኙ ኢትዮጵያውያን እየተነዛና እየተሰበከ ባለው ጥላቻና ግጭትን የመቀስቀስ ዓላማ ያዘለ ፕሮፖጋንዳ አኳያ፣ ወቅታዊውን የኢትዮጵያውያን ሙስሊሞች የሃይማኖት ነፃነትን የማስከበር ሰላማዊ ትግል በአጭሩ በማስቃኘትና፣ በአሁኑ ወቅት መንግሥትና አጫፋሪዎቹ እያካሄዱ ያሉትን ህዝብን ከህዝብ ለማጋጨት ያለመ ዕኩይ ዘመቻ አደገኛነት በማመላከት ዓላማ የተዘጋጀ ነው፡፡ የኢትዮጵያ ዳያስፖራ ራዲዮ ያቀረበውን ዝግጅት አሉታዊነት በድፍኑ ከመተቸት ይልቅ፣ በዝግጅቱ ይዘት ላይ ያተኮረ ሰፋ ያለ ሒስ ማቅረብ አስፈላጊ ይመስለናል፡፡ እናም በዚህ ጽሑፍ የራዲዮ ጣቢያው ባቀረበው ዝግጅት ይዘት ጥቂት አንኳር ጉዳዮች ላይ በማተኮር የጣብያውን አሳዛኝና አሳፋሪ ሥራ ለማስቃኘት እንሞክራለን፡፡
ምሥጢራዊ ሰነዶችና ይፋ የመውጣታቸው ፖለቲካዊ አንድምታ
የዳያስፖራው ራዲዮ “በኢትዮጵያ ፖለቲካዊ እስልምና እየተስፋፋ ነው” የሚል ክስ ያቀርባል፡፡ ለዚህ ክሱ ካቀረባቸው ማስረጃዎች መካከል ‹ዊኪሊክስ› የተሰኘው የዊሊያም አሳንጅ ድረ‑ገፅ ይፋ ያደረጋቸውን ከስቴት ዲፓርትመንት ያፈተለኩ ምሥጢራዊ ሰነዶች ይገኙበታል፡፡ እንደ ማስረጃ በተጠቀሱት ‹ዊኪሊክስ› ይፋ ያደረጋቸው ሰነዶች ይዘት ላይ ከማተታችን በፊት ግን፣ የእነዚህ ሰነዶች ከስቴት ዲፓርትመንት ዳታቤዝ ተሠርቆ በ‹ዊኪሊክስ› ድረ‑ገፅ ይፋ የመደረጉን ፖለቲካዊ አንድምታዎች መመልከት ተገቢ ይመስለናል፡፡
እንደሚታወቀው፣ ማንኛውም መንግሥት በ“ጥብቅ ምስጢር”ነት የሚይዛቸው ጉዳዮች ይኖሩታል፡፡ እንዲህ ዓይነት ሰነዶች “ጥብቅ ምስጢር” (CLASSIFIED) በሚል ተፈርጀው በጥንቃቄ ይቀመጣሉ፡፡ በመንግሥት ሥራ ላይ አንድን ጉዳይ “ጥብቅ ምስጢር” የሚያደርጉ ተቀባይነት ያላቸው ምክንያቶች ሊኖሩ ይችላሉ፡፡ በሌላ በኩል አንዳንድ ጉዳዮች/ሰነዶች በ“ጥብቅ ምስጢር”ነት የሚይያዙት ይፋ ቢሆኑ ጉዳዩ ከሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት ተቃውሞን ሊያስነሱ፣ ጠንካራ ትችትና ውግዘት ሊያስከትሉ እንደሚችሉ ስለሚታወቅ ነው፡፡ በ“ጥብቅ ምስጢር”ነት የሚያዙ ጉዳዮች/ሰነዶች ይፋ መውጣት ብሄራዊ እና/ወይም ዓለምአቀፍ ሕግን መሠረት ያደረገ ተጠያቂነትን ሊያስከትል፣ ወይም ደግሞ እንደ ይዘቱ በአገራት ግንኙነት ላይ አሉታዊ ተፅዕኖ ሊያሳድር ይችላል፡፡ ከጉዳዩ ጋር ተያያዥ የሆኑ ኦፊሴላዊ የ“ጥብቅ ምስጢር” ሰነዶች ጉዳዩ የሚመለከታቸው አካላት ጋር ከደረሱ፣ እንደሁኔታው በምሥጢር ሊካሄዱ የታቀዱ መርኃ‑ግብሮችን ሊያሰናክሉም ይችላሉ፡፡
በብዙ አጋጣሚዎች መንግሥታት፣ ይበልጡኑም በከፍተኛ የሥልጣን እርከን ላይ ያሉ ፖለቲከኞች ዕውን ሊያደርጉ የሚሹትና በአደባባይ ለህዝብ የሚናገሩት ፍፁም ለየቅል ሊሆን ይችላል፡፡ በእንዲህ ዓይነት ጉዳዮች ላይ የአንድን መንግሥት ተግባራት እውነተኛ መግፍዔ (Motive) ለማወቅ፣ አልያም የቅርብ ግምት ለመስጠት የሚቻለው በጥልቅ ፖለቲካዊ ትንተና ነው፡፡ … በዓለምአቀፍ የቴሌቪዥን ኔትወርኮች ዘወትር እንደምናየው፣ የአንድን መንግሥት እርምጃዎች፣ ውሳኔዎች ወይ የአቋም ለውጦች ከተለያዩ ማዕዘናት በመዳሰስ በይፋ ያልተነገሩ ብዙ መረጃዎችን የሚሰጡት የፖለቲካ ተንታኞች ናቸው፡፡ ግና ከጉዳዩ ጋር ቀጥተኛ ግንኙነት ያለው በ“ጥብቅ ምስጢር”ነት የተያዘ የመንግሥት ሰነድ ድንገት ሾልኮ ቢወጣስ? ይህ ሲሆን፣ የፖለቲካ ተንታኙን የዙርያ‑ገብ ትንተና ድካም በመቀነስ፣ በቀላሉ ወደ እውነተኛው የጉዳዩ ምንነት ያደርሳል፡፡ በ“ጥብቅ ምስጢር”ነት የተያዘ የመንግሥት ሰነድ ይፋ መውጣት እንደ ጉዳዩ የክብደት ደረጃ አንድን መንግሥት በከፍተኛ ኃፍረት አልያም ቅሌት ውስጥ ሊከተውም ይችላል፡፡
በዚህ ማዕቀፍ የኢትዮጵያ ዳያስፖራ ራዲዮ ጣቢያ ባቀረበው ዝግጅት በስፋት ያጣቀሳቸውን በ‹ዊኪሊክስ› ይፋ የተደረጉ የስቴት ዲፓርትመንት “ምስጢራዊ ሰነዶች” በምን መልኩ ለዕኩይ ዓላማ እንደዋሉ ስናይ በጣም እንገረማለን፡፡ … እናዝናለንም፡፡
ዊኪሊክስ” ማንን እና ምንን ነው ያጋለጠው?
በመሠረቱ፣ ዊኪሊክስ ይፋ ያደረጋቸው የስቴት ዲፓርትመንት “ምሥጢራዊ ሰነዶች” በአሁኑ ወቅት ሙስሊም ኢትዮጵያውያን እያካሄዱ ከሚገኙት ሕገ‑መንግሥታዊ የሃይማኖት ነፃነትን የማስከበር ትግል ጋር ምንም ዓይነት ቀጥተኛ ግንኙነት የላቸውም፡፡ በአንጻሩ ግን “ምሥጢራዊ ሰነዶቹ” የኢሕአዴግ መንግሥት ካለፉት ጥቂት ዓመታት ወዲህ በኢትዮጵያውያን ሙስሊሞች የሃይማኖት ነፃነት ላይ የከፈተው ግብታዊነት የሚታይበት “የጥሰት ዘመቻ”፣ የአሜሪካ መንግሥት “አሳስቦኛል” ከሚለው አንድ ጉዳይ ጋር ተያያዥነት ሳይኖረው እንዳልቀረ ይጠቁማሉ፡፡ ሰነዶቹ ከምንም በላይ ዛሬ የኢሕአዴግ መንግሥት ከህዝበ‑ሙስሊሙ ጋር የተፋጠጠበት ጉዳይ፣ በኢትዮጵያዊ ዓይን የታየ ሳይሆን፣ በአሜሪካ መንግሥት ዓይን የታየ፣ በአሜሪካዊኛ የተተነተነ፣ በአሜሪካ ልዩ ፍላጎት ላይ ተመሥርቶ የተቃኘ መሆኑን ነው በግልፅ የሚያሳዩት፡፡ … ይህ ሆኖ ሳለ፣ የዳያስፖራ ራዲዮ ጣቢያ፣ የአሜሪካ መንግሥት በራሱ ምክንያት ምሥጢር አድርጎ ሊይዝ ይፈልገው የነበረውን ይህን ሰነድ በማጣቀስ፣ ወቅታዊውን የኢትዮጵያውያን ሙስሊሞች የሃይማኖት መብትን የማስከበር ሰላማዊ እንቅስቃሴ ለማጠልሸት ዓላማ አውሎታል፡፡ ይህ በአንድ በኩል በጣም የሚያስቅና የጣቢያውን ብስለት-የለሽነት የሚያሳይ ሲኾን፣ በሌላ በኩል ሙስሊም ኢትዮጵያውያን የፍትኅና የነፃነት ተሟጋቾች (አክቲቪስቶች) ከአንድ ዓመት በፊት በፌስቡክ ላይ እንደነገሩ ነካክተው ያለፉትን ነገር ዛሬ ጠበቅ አድርገን እንድንመለስበት የጋበዘ በመሆኑ የሚመሰገን ነው፡፡
እስከምናውቀው ድረስ፣ ዊኪሊክስ ይፋ ያደረጋቸው አዲስ አበባ ከሚገኘው የአሜሪካ ኤምባሲ ወደ ስቴት ዲፓርትመንት የተላለፉ “ምሥጢራዊ ሰነዶች” በቁጥር ሦስት ሲኾኑ፣ ሦስቱም እ.አ.አ በኦገስት 2009 (በኢት. አቆጣጠር በነሐሤ 2001) የተዘጋጁ ናቸው፡፡ እነዚህ ሰነዶች፣ የኢሕአዴግ መንግሥት በኢት. አቆጣጠር በሐምሌ 2003 በይፋ የጀመረው የአህባሽ አስተምህሮን በህዝበ‑ሙስሊሙ ላይ የመጫን መርኃ‑ግብር፣ ከዚያ ሁለት ዓመታት ቀደም ብሎ የአሜሪካ መንግሥት በዊኪሊክስ ላይ ባንፀባረቀው በጥልቀት ያልተተነተነ ስጋት ላይ የተመሠረተ መሆኑን ነው ያጋለጡት፡፡ … እነዚህ “ምሥጢራዊ” የነበሩ ሰነዶች በይዘታቸው በአሁኑ ወቅት የኢህአዴግ መንግሥት በኢትዮጵያውያን ሙስሊሞች ላይ እያካሄደ የሚገኘው የአገሪቱን ሕገ‑መንግሥት የሚጻረር (የሃይማኖት ነፃነትን የመገደብ) መርኃ‑ግብር በእውነትና በእውቀት ላይ የተመሠረተ ከመሆን ይልቅ፣ የአሜሪካ መንግሥት ከራሱ ዕይታ ያንፀባረቀው፣ ኢሕአዴግ በጥልቀት ሳያጠናውና ጉዳዩ ከሚመለከታቸው ሙስሊም ዜጎቹ (ቢያንስ ከሚያምናቸው ሙስሊም ምሁራን) ጋር ሳይማከርበት ዓይኑን ጨፍኖ በግብታዊነት ሊያስፈጽም የተቀበለው የቤት ሥራ መሆኑን ነው በግልፅ የሚያሳዩት፡፡ ዊኪሊክስ ምሥጢራዊ ሰነዱን ይፋ ባያደርግ ኖሮ፣ የአሜሪካ መንግሥት እ.አ.አ እስከ 2019 (በኢት. አቆጣጠር እስከ ነሐሤ 2011) ድረስ ይህንን ሐቅ በምሥጢር ሊይዘው ነበር የፈለገው፡፡ ምናልባት ሰነዱን ምሥጢር ማድረግ የተፈለገው ተግባሩ በሃይማኖት ጉዳይ ጣልቃ እንደመግባት ሊቆጠር ይችላል ከሚል ስጋት በመነጨ ሊሆን ይችላል፡፡
የኢትዮጵያ ዳያስፖራው ራዲዮ “እኛ” በተሰኘ ፕሮግራሙ፣ በዊኪሊክስ ይፋ በመደረጋቸው የአሜሪካ መንግሥትና ኢሕአዴግ የተጋለጡባቸውን እኒህኑ በምሥጢር ተይዘው የነበሩ ሰነዶች ዋቢ በማድረግ ሙስሊም ኢትዮጵያውያን በሃይማኖታዊ ነፃነታቸው ላይ የተቃጣውን ጥሰት በመቃወም የሚያካሂዱትን ሰላማዊ ትግል ሊያጠለሽ ይሟሟታል፡፡ የራዲዮ ጣቢያው ዝግጅት ከአገረ‑አሜሪካ ለሚገኝ ዳረጎት ሲሉ የ“አክራሪነት”ን ነጋሪት እየጎሰሙ ሙስሊሙን ዜጋ ቁም ስቅል የሚያሳዩት ገዢዎቻችን የተጋለጡበትን “የአደባባይ ምሥጢር” እየተረከ፣ በአገሪቱ ሕገ‑መንግሥት ስለተደነገገው የሃይማኖት ነፃነታቸው መከበር የሚጮሁ ኢትዮጵያውያን ሙስሊሞችን በ‘ፖለቲካዊ እስልምና’ አስፋፊነት በመወንጀል ሊያሸማቅቅ ይሞክራል፡፡ በሌላም በኩል፣ የሙስሊም ኢትዮጵያውያንን ሕጋዊ፣ ፍትኃዊና ሰላማዊ ጥያቄ ደግፈው የቆሙ ሙስሊም ያልሆኑ ወገኖቻችንን ግንዛቤ ለማዛባትና የሙስሊም ወገኖቻቸውን ሰላማዊና ሕጋዊ ትግል በጥርጣሬ እንዲመለከቱት ለማድረግ ይተጋል፡፡ በዚህ ብቻ ግን አያበቃም፤ ከጥቂት ዓመታት በፊት በአገራችን አንድ ክፍል በተከሰተ የማንም አዕምሮ የማይቀበለው ግጭት ላይ የደረሱ ጥፋቶችን፣ ስሜት በሚኮረኩሩ የድምፅ ግብዓቶች አጅቦ በማቅረብ፣ ሙስሊም ያልሆኑ ኢትዮጵያውያን በሙስሊም ወገኖቻቸው ላይ ጥላቻና ጥርጣሬ እንዲያድርባቸው የሚገፋፋ መሠሪ ፕሮፖጋንዳ ይነዛል፡፡ እግረ መንገዱንም፣ ወቅታዊውን የሙስሊም ኢትዮጵያውያን ሰላማዊ የመብት ትግል ስውር ዓላማ ያለው ለማስመሰል ዳር ዳር ይላል፡፡
በቀድሞው የአሜሪካ አምባሳደር ዶናልድ ያማሞቶ አማካይነት የተዘጋጀውና ዊኪሊክስ ይፋ ያደረገው የመጀመርያው ሰነድ ‹‹GROWING WAHABI INFLUENCE IN ETHIOPIA: AMHARA›› የሚል ርዕስ አለው፡፡ ሰነዱ አዲስ አበባ የሚገኘው የአሜሪካ ኤምባሲ የህዝብ ጉዳዮች ክፍል (Public Affairs Section) ኃላፊዎች በአማራ ክልል፣ ደሴ አቅራቢያ በሚገኙ የገጠር ወረዳዎች (እ.አ.አ. ከጁን 3‑5፣ 2010) ባካሄዱት የሦስት ቀናት ቅኝት ላይ ተመሥርቶ የተዘጋጀ ነው፡፡ የኤምባሲው ባልደረቦች ይህን ቅኝት ያካሄዱት ከአንድ የዞን መሥተዳድር ኃላፊ ጋር መሆኑም በሰነዱ ላይ ተጠቁሟል፡፡ …
ሰነዱ በአማራ ክልል ‹ወሃቢያ› የተባለው የእስልምና አስተምህሮት እየተስፋፋ መሆኑን፣ በገጠር ከተሞች በርካታ መስጊዶች ከኩዌት መንግሥታዊ ያልሆኑ ድርጅቶች በተገኘ ፈንድ መታነፃቸውን፣ የኤምባሲው ኃላፊዎች በጎበኟቸው አካባቢዎች የሚኖሩ ሙስሊም ሴቶች ሃይማኖታዊ አለባበስ በመከተል ፊታቸውን እንደሚሸፍኑ፣ ወንዶች ደግሞ ሱሬያቸውን እንደሚያሳጥሩ፣ ፂማቸውን ግን እንደማያሳድጉ ወዘተ. ይጠቃቅሳል፡፡ በተጨማሪም፣ የወሃቢያ አስተምህሮ የነቢዩ ሙሐመድን ልደት (መውሊድ) ማክበርን ስለሚቃወም፣ በዚህ ረገድ በወሃቢ አስተምህሮና በሱፊ አስተምሀሮ ተከታዮች መካከል፣ በተለይ የሱፊ እስልምና ተከታዮች መውሊድን በሚያከብሩበት የጀማ ንጉስ መስጂድ አካባቢ ከዚያ ቀደም ባለ ጊዜ ሁኔታው ወደ ግጭት አምርቶ እንደነበረ ይገልፃል፡፡ አክሎም የሱፊ እስልምና ተከታዮች የመውሊድ በአልን ለሚያከብሩበት የጀማ ንጉስ መስጂድ እድሳት በማድረግ ባህላዊ ቅርሱን ስለመጠበቅ አስፈላጊነት ያወሳል፡፡ ለዚህም አሜሪካ ከአምባሳደሩ የባህላዊ ቅርሶች ጥበቃ ፈንድ ድጋፍ የማድረግ ፍላጎት እንዳላት ይጠቁማል፡፡ [http://wikileaks.org/cable/2009/07/09ADDISABABA1672.html#]
ሰነዱ የኤምባሲው የስራ ኃላፊዎች ለሦስት ቀናት ባካሄዱት ቅኝት፣ ከአካባቢው መስተዳድር የሥራ ኃላፊ እንዲሁም ከወቅቱ የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት (መጅሊስ) በተገኘ መረጃ ላይ ተመሥርቶ፣ በኢትዮጵያ የወሃቢ አስተምህሮ መስፋፋት ለዘመናት የቆየው የተለያዩ ሃይማኖት ተከታዮች የመቻቻል ዕሴት አደጋ እንደተደቀነበት ይጠቅሳል፡፡ ሰነዱ በገፅ 3 [8.(C)] በዚህ ጉዳይ ላይ ጠቅላይ ምክር ቤቱን ሲጠቅስ እንዲህ ይላል፡‑
the IASC continues to be very concerned about growing Wahabi influence in Ethiopia. The newly appointed Council is decidedly anti-Wahabi and speaks openly of their concern about Wahabi missionaries and their destabilizing influence in Ethiopia.
ሰነዱ በገፅ 4 (13.(C)) ላይ ደግሞ የመጅሊሱን ኃላፊዎች ዋቢ በማድረግ በወቅቱ (እ.አ.አ. በ2010) መጅሊሱ ከወሃቢ አስተምህሮ ተከታዮች እንደፀዳ ይጠቅሳል፡፡
13. (C) In a shift from past practice, the IASC is now completely purged of Wahabi members. […] the Council members acknowledged that the Council is now all Sufi and in their public statements they repeatedly make reference to Ethiopia’s tradition of religious tolerance and co-existence with the Christian communities.
በተጨማሪም በዚሁ ገፅ ላይ፣ የእስልምና ምክር ቤቱ [የአመራር] አባላት በመንግሥት እንደሚሾሙ በግልፅ ይናገራል፡‑
As the Ethiopian government appoints the members of the Islamic Council, it is clear that the GoE shares this concern about growing Wahabi influence and is supporting moderate Muslim leaders in trying to counter that influence.
እዚህ ላይ ልብ ሊባል የሚገባው ቁም ነገር የመላው ኢትዮጵያውያን ሙስሊሞች የጋራ ተቋም እንደሆነ በሚታሰበውና ለረዥም ጊዜያት የሱፊና የሰለፊ አስተምህሮ ተከታዮች በጋራ ሲያስተዳድሩት በኖረው መጅሊስ ላይ፣ በዚህ ወቅት (እ.አ.አ. በ2010) መንግሥት ሙሉ በሙሉ የአህባሽ አስተምህሮ ተከታዮችን የሾመ መሆኑ ነው፡፡ የአህባሽ አስተምህሮ፣ ከሰለፊ አስተምህሮ ጋር የከረረ ተቃርኖ እንዳለው የሚታወቅ ሲኾን፣ በሰለፊ አስተምህሮ ተከታዮች ላይም እጅግ የመረረ ጥላቻ ያንፀባርቃል፡፡ ከዚህ በላይ በጠቀስነው የዊኪሊክስ ሰነድ ላይ እንደተመለከተው፣ መንግሥት በጠቅላይ ምክር ቤቱ ላይ የአህባሽ አስምህሮ ተከታዮችን የሾመው ለዘብተኛ ሙስሊሞችን በመደገፍና የወሃቢን ተፅዕኖ ለመቋቋም ነው ተብሏል፡፡ ይህም ‹‹እርምጃው የወሃቢ አስተምህሮ በሃይማኖቶች የመቻቻል እሴት ላይ ደቅኖታል የሚባለውን ስጋት የማስወገድ ዓላማ ያለው ነው›› የሚል አንድምታ አለው፡፡ ነገር ግን እውን ሐቁ ያ ነዉን? የወሃቢ አስተምህሮ ደቅኖታል የተባለውን ስጋት የማስወገጃው መንገድስ ይህ ነውን? ብለን ስንጠይቅና … መሬት ላይ ያለውን ሐቅ ስንፈትሽ የምናገኘው ምላሽ ይህንን አያረጋግጥልንም፡፡ [ለዚህ አባባላችን ዋቢ የሚሆኑ ተግባራዊ ምሳሌዎችን ወደኋላ ላይ እናቀርባለን፡፡]
ዊኪሊክስ ይፋ ባደረጋቸው ሰነዶች ላይ፣ የአሜሪካ መንግሥት የሱፊ ስርዓተ‑አምልኮ የሚከናወንባቸውን ጥንታዊ መስጂዶችና የቅዱሳን የመቃብር ሥፍራዎችን ጠብቆ በማቆየት ዓላማ መሠራት አለባቸው ብሎ የሚያምናቸው ተግባራት ተጠቅሰዋል፡፡ … የአሜሪካ መንግሥት በኢትዮጵያ በተለያዩ ሃይማኖት ተከታዮች መካከል ፀንቶ የኖረው የመቻቻል ባህል በዘላቂነት ይቀጥል ዘንድ የራሱን ጥረት ለማድረግ በመሻቱ ሊመሰገን እንጂ ሊወቀስ አይገባውም፡፡ ነገር ግን፣ እንዲህ ዓይነቱ ጥረት፣ የቱንም ያህል ቀና ቢሆን እንኳ፣ ጉዳዩን እጅግ በቅርበትና በጥልቀት መመርመር የሚጠይቅ መሆኑ አይካድም፡፡ ከዚያም በላይ ግን፣ የጉዳዩ ባለቤት የሆነውን ማኅበረሰብ፣ ከማኅበረሰቡም ተደማጭነት ያላቸውን የእምነቱ መሪዎች ወይም የሃይማኖቱን ሊቃውንት ባላካተተ መልኩ ሲካሄድ የሚፈለገውን አዎንታዊ ውጤት ያመጣል የሚል እምነት የለንም፡፡ በየትኛውም የሃይማኖት ማኅበረሰብ ውስጥ ከእምነት‑ተኮር አስተሳሰብ ጋር ተያያዥነት ያላቸው ልዩነቶች ሊፈጥሩ የሚችሉትን አላስፈላጊ ፍጥጫና ይህም ሊያስከትል የሚችለውን አሉታዊ ውጤት በማስቀረት ጥረት ውስጥ የጉዳዩ ባለቤት የሆነው የሃይማኖት ማኅበረሰብ እና ተደማጭ መሪዎቹ ያላቸው ሚና በምንም የሚተካ አለመሆኑ ሊሰመርበት ይገባል፡፡ የወሃቢያ መስፋፋትም ሆነ ከሱፊያ አስተሳሰብ ተከታዮች ጋር ያሉ ልዩነቶችንና ከልዩነቶቹ ሊመነጩ ይችላሉ ተብለው የሚታሰቡ ውጥረቶችን በዘላቂነት ለመፍታትም የጉዳዩ ባለቤቶችን የመፍትኄ አካል በማድረግ ፈንታ የችግር ምንጭ አድርጎ ማሰብ ትክክለኛ ነው ብለን አናምንም፡፡
ወሃቢያ እንደ ስጋት …
ለመሆኑ የአሜሪካ መንግሥት በኢትዮጵያ እየተስፋፋ ነው የሚለውን የ‹ወሃቢ› አስተምህሮ ከምን አኳያ ነው እንደ ስጋት የተመለከተው? … ይህ ስጋት በመሬት ላይ ያለ ነውን? ካለስ ስጋቱን የማስወገጃው መንገድ ምንድን ነው? … ሙስሊም ኢትዮጵያውያንስ ይህን ስጋት በማስወገድ ረገድ ያላቸው አቋምና አስተሳሰብ ምን ይመስላል? … በተግባርስ ይህን ስጋት ለማስወገድ ምን አድርገዋል? … ‘ዊኪሊክስ’ ይፋ ያደረጋቸውን “ምስጢራዊ ሰነዶች” መነሻ አድርጎ ስለ ‘ፖለቲካዊ እስልምና በኢትዮጵያ’ ሀተታ ያቀረበው የዳያስፖራ ራዲዮ እነዚህን ቁልፍ ጥያቄዎች አልጠየቀም፡፡ ባለመጠየቁም በኢትዮጵያ መሬት ላይ ያለውን ተጨባጭ ሁኔታ አላየም፡፡ ከዚያ ይልቅ፣ ሰነዱን ላለፉት ሁለት ዓመታት ገደማ ሙስሊም ኢትዮጵያውያን እያካሄዱ ያሉትን ሃይማኖታዊ ነፃነትን የማስከበር ሰላማዊ ትግል ጥላሸት ለመቀባት ዓላማ አውሎታል፡፡
በእኛ እምነት በየትኛውም ሃይማኖት ውስጥ የሚንፀባረቁ የጽንፈኝነት ዝንባሌዎችን ማረቅ የሚቻለው ትምህርትና እውቀትን በማስፋፋት ብቻ ነው፡፡ በዚህም መንፈስ በኢትዮጵያ ሙስሊም ማኅበረሰብ ውስጥ የአገሪቱ ሙስሊሞች የጋራ ተቋም ከሚሰኘው መጅሊስ ይልቅ የሃይማኖቱ ምሁራን በርካታ አዎንታዊ ተግባራትን ሲያከናውኑ ቆይተዋል፡፡ ከአስተምህሮ ልዩነቶች የሚመነጩ ውጥረቶችን ከማስወገድ አኳያም አንዱን ወገን በጽንፈኝነት ፈርጆ የማሳደድን አማራጭ ከሚያራምደው የመንግሥትና የመንግሥታዊው መጅሊስ መንገድ ይልቅ፣ የሙስሊሙ ማኅበረሰብ አንጋፋ የሃይማኖት ሊቃውንት በጥልቅና በሳል ውይይቶች አማካይነት ኅብረተሰቡን ወደጋራ መግባባት ለማምጣት በርካታ አዎንታዊ ሥራዎችን አከናውነዋል፡፡ በኢትዮጵያ አቆጣጠር ከ2000/2001 የተለያዩ አስተምህሮ የሚከተሉ አንጋፋ የሙስሊም ሊቃውንት፣ በሱፊው በኩል በሸኽ ዑመር ኢድሪስ መሪነት፣ በሰለፊ በኩል ደግሞ በዶ/ር ጀይላን መሪነት፣ ይህን በመሰሉ ጉዳዮች ላይ ተከታታይ የሆኑ በሳል ውይይቶችን በማድረግ ከመግባባት ላይ ደርሰው፣ የአንድነት ጉባዔ ለማካሄድ የመጨረሻ ዝግጅት እያካሄዱ ነበር፡፡ ይህን መሰል ታላቅ አዎንታዊ እርምጃ ከኢትዮጵያ በቀር በሌሎች ሙስሊሞች በሚበዙባቸው አገራት እንኳ መካሄዱ ያጠራጥራል፡፡ ግና ይህ የኢትዮጵያውያን ሙስሊሞች የተለየ አዎንታዊ ተግባር በህዝብ ባልተመረጠው የእስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት አመራሮችም ሆነ በመንግሥት ዘንድ በበጎ ዓይን አልታየም፡፡ እናም መንግሥት እና ምክር ቤቱ ይህንን ሰላምና አንድነትን የማምጣት ዓላማ የነበረውን ሂደት ሆን ብለው አስተጓጉለውታል፡፡ ከቶ ይህ ለአገር እና ለህዝቦች ሰላም የማሰብ ተግባር ነውን? መልሱን ቅን ልቦና ላላቸው ወገኖች ኅሊና ትተነዋል፡፡
በሙስሊሙ ኅብረተሰብ መካከል የሚፈጠሩ የሃይማኖት አስተምህሮን መሠረት ያደረጉ ማናቸውም ችግሮች ሙስሊሙ ኅብረተሰብ በራሱ ሊፈታቸው የሚገባ፣ የውስጥ ጉዳዮቹ ናቸው፡፡ የጋራ ተቋማችን በምንለው የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ላይ በመንግሥት የተሾሙ አመራሮች ይህንን የማድረግ ኃላፊነታቸውን አለመወጣታቸው ሳያንስ፤ ጭራሽ በዚህ መንፈስ ይካሄዱ የነበሩ የሙስሊም ሊቃውንት ውይይቶችን ማሰናከላቸው እየታወቀ፣ የኢሕአዴግ መንግሥትን እና በእርሱ ሹማምንት የሚመራውን መጅሊስ ፀረ‑አክራሪ፣ ህዝበ ሙስሊሙን ግን የፖለቲካዊ እስልምና አስፋፊ አድርጎ ለመሳል የሚደረገው ሙከራ በጣም የሚያሳዝን እና የሚያስተዛዝብ ነው፡፡
ስለ እኛ ማን ይናገር …
ዊኪሊክስ ይፋ ያደረጋቸው የስቴት ዲፓርትመንት የ2010 ሰነዶችን ዋቢ በማድረግ በዳያስፖራ ራዲዮ በ‘ፖለቲካዊ እስልምና’ ዙርያ በቀረበው ዝግጅት ላይ የምናቀርበው ሌላው ዐብይ ሒስ፣ ለኢትዮጵያውያን ወገኖቻችን ስለ ሙስሊም ኢትዮጵያውያን ማንነትና ምንነት ማን ነው የሚነግራቸው በሚል ጥያቄ ላይ የተመሠረተ ነው፡፡ በእኛ እምነት ሙስሊም ላልሆኑ ኢትዮጵያውያን ወገኖቻችን ስለ ሙስሊም ኢትዮጵያውያን ማንነትና ምንነት በሦስተኛ ወገን ሊነገራቸው አይገባም፡፡ መንግሥታችን የገዛ ዜጎቹን፣ ሙስሊም ያልሆኑ ወገኖቻችንም ለዘመናት አብረናቸው የኖርን ሙስሊም ወገኖቻቸውን በውጭ መንግሥት ዕይታ፣ ግንዛቤ፣ አረዳድና አስተሳሰብ ላይ ተመሥርተው ሊያዩን ይገባል ብለንም በፍፁም አናምንም፡፡ በእኛ እምነት ይህ ለዘመናት አብሮ በመኖር ያጎለበትነውን ተዋድዶ፣ ተፋቅሮና ተከባብሮ የመኖር ታላቅ እሴት ትርጉም‑አልባ የሚያደርግ የተሳሳተ አካሄድ ነው፡፡ …
**********
በኢትዮጵያ፣ ከቅርብ ጊዜያት ወዲህ በህዝብ ሀብት የሚንቀሳቀሱትና ሙሉ በሙሉ በኢሕአዴግ ቁጥጥር ሥር ያሉት መገናኛ ብዙኃን፣ እንዲሁም ከከፍተኛ የመንግሥት ባለሥልጣናት አንስቶ እስከ ወረዳና ቀበሌ ድረስ ያሉ የኢሕአዴግ ካድሬዎች፣ “ወሃቢ!” የሚለውን ስያሜ ህዝብን፣ በተለይም ሙስሊም ያልሆኑ ወገኖቻችንን የሚያስፈራሩበት ጭራቅ አድርገውታል፡፡ … ከኩዌት መንግሥት በተገኘ የገንዘብ እርዳታ መስጊዶች መገንባታቸው አልያም አሮጌ መስጊዶች መታደሳቸው የወሃቢ እምነት መስፋፋቱን ይገልጻል ብሎ መደምደም የሚቻል አይመስለንም፡፡ በአዲስ አበባ ፒያሳ አቅራቢያ የሚገኘው ኑር (በተለምዶ በኒ) መስጂድ ከኩዌት በጎ አድራጊዎች በተገኘ የገንዘብ እርዳታ ነው ፈርሶ በአዲስ መልክ የተገነባው፡፡ ነገር ግን መስጂዱ የአንድ የተለየ አስተምህሮ ማስፋፊያ አይደለም፡፡
በምሥጢራዊ ሰነዱ ላይ ባህላዊ ወረራ በማስፋፋት የተጠቀሰችው ሳዑዲ አረቢያ፣ ከኢትዮጵያም በላቀ መልኩ ለዩናይትድ ስቴትስ ወዳጅ መሆኗ ይታወቃል፡፡ ምናልባትም ሰነዱን ምስጢራዊ (Classified) ተብሎ እንዲፈረጅ ካደረጉት ነጥቦች አንዱ፣ “የሳዑዲ ባህላዊ ኢምፔሪያሊዝም” ‘ያሳስበኛል’ የሚለው የአሜሪካ መንግሥት በባህላዊ ኢምፔሪያሊዝም አስፋፊነቷ ከሚያማት አገር ጋር ባለው ወዳጅነት አኳያ ሰነዱ በሚያንፀባርቀው ተቃርኖ ላይ የተመሠረተ ይመስለናል፡፡
ዩናይትድ ስቴትስ ኢትዮጵያን ጨምሮ የአፍሪካ ቀንድ አካባቢ ሰላምና ፀጥታ ለምን ያሳስባታል አንልም፡፡ ነገር ግን እኛ ኢትዮጵያውያን ሙስሊሞች ለቀጣናውም ሆነ በይበልጥም ለአገራችንና ለመላው ህዝቧ ሰላም፣ ዕድገትና ብልፅግና ያለን መቆርቆር ከዩናይትድ ስቴትስ መንግሥት የበለጠ እንጂ ያነሰ እንዳልሆነ ማንም ሊዘነጋው አይገባም፡፡ የአገራችን ሰላም፣ ፀጥታና ደኅንነት ቢረጋገጥ፣ ከሌሎች ወገኖቻችን ጋር የእነዚህ ዕሴቶች ትሩፋት በሆነው ዕድገትና ብልፅግና ተጠቃሚዎቹ ኢትዮጵያውያን ሙስሊሞችም ነን፡፡ በአንፃሩ፣ የእነዚህ ዕሴቶች መጓደል ከሌሎች ወገኖቻችን ጋር ኢትዮጵያውያን ሙስሊሞችንም ጭምር ነው የሚጎዳው፡፡
ኢትዮጵያውያን ሙስሊሞች ሃይማኖታችን ኢስላም የአገራችንን ሰላም የሚያውክ የየትኛውም የውጭ ኃይል መሣርያ እንዲሆን የምንፈቅድ ዜጎች አይደለንም፡፡ ነገር ግን በተለምዷዊ አሉታዊ ዕይታ፣ ሃይማኖታችን ኢስላምም ሆነ ተከታዮቹ ሙስሊሞች በድፍኑና በጭፍኑ የችግር ምንጮች ተደርገን መታሰብንም አንቀበልም፡፡ ኢትዮጵያውያን ሙስሊሞች ከሃይማኖታችን ጋር ተያይዞ ለሚነሳ፣ ወይም ይነሳል ተብሎ ለሚታሰብ ማንኛውም ችግር የመፍትኄ አካል እንጂ የችግር ምንጭ አይደለንም፡፡ እዚህ ላይ ፕሬዚደንት ባራክ ኦባማ እ.አ.አ ጁን 4 ቀን 2009 በካይሮ ዩኒቨርሲቲ፣ ግብፅ፣ ተገኝተው ለሙስሊሙ ዓለም ከደረጉት ታሪካዊ ንግግር ላይ መጥቀስ እንወዳለን፡‑ “ኢስላም ነውጠኛ ጽንፈኝነትን ለመዋጋት በሚደረገው ትግል ሰላምን እውን ለማድረግ የሚያግዝ አጋር እንጂ፣ ከቶም የችግሩ አካል አይደለም፡፡”
ፕሬዚደንት ኦባማ በዚሁ የካይሮ ታሪካዊ ንግግራቸው፣ “አንድን ንፁህ ነፍስ የገደለ፣ መላውን የሰው ልጅ እንደገደለ ነው፡፡ አንድን ንፁህ ነፍስ በግፍ ከመገደል ያዳነ መላውን የሰው ልጅ ያዳነ ያህል ነው” የሚለውን ቁርአናዊ ቃል ጠቅሰውታል፡፡ ይህ ቁርአናዊ ቃል ምንጊዜም ህያው ነው፡፡ ፕሬዚዳንቱ በዚሁ መድረክ ላይ እንደተናገሩትም፣ “ከአንድ ቢሊዮን የሚበልጡ ተከታዮች ያሉትን ዘመናትን ያስቆጠረ እምነት ከጥቂቶች ጠባብ እና በጥላቻ ላይ የተመሠረተ እንቅስቃሴ እጅግ የገዘፈ” የመሆኑ እውነታ ከቶውንም ሊዘነጋ አይገባም፡፡
የዊኪሊክስ ሰነዶች ይፋ ያደረጋቸው አዎንታዊ ነጥቦች
በዊኪሊክስ ላይ ይፋ ከተደረገውና የአሜሪካ መንግሥት፣ በአዲስ አበባው ኤምባሲው አማካይነት ካስተላለፈው መልዕክት ውስጥ የኢትዮጵያውያን ሙስሊሞች ሃይማኖታዊ ትውፊቶችና ቁሳዊ ቅርሶችን ከጥፋት ለመታደግ አስቦ ያከናወናቸው ተግባራት ተጠቅሰዋል፡፡ እኛ ኢትዮጵያውያን ሙስሊሞች በዚህ የአሜሪካ መንግሥት ተግባር በጣም ደስተኞች ከመሆናችንም በላይ ምስጋናችንም ከፍተኛ ነው፡፡ በእርግጥም፣ ጠንካራ የሃይማኖት ተቋም ቢኖረን ኖሮ፣ ይህ በእኛው ተቋም ሊፈፀም ይገባው የነበረ እጅግ ትልቅ ተግባር ነበር፡፡ እኛ ልንሠራው ይገባን የነበረውን ሥራ የአሜሪካ መንግሥት በራሱ ተነሳሽነት ስላከናወነልን እጅግ ትልቅ ውለታ እንደዋለልን ሳናወሳ አናልፍም፡፡
**************
ከቅርብ ጊዜያት ወዲህ በላይኛው የሥልጣን እርከን ላይ ካሉ የመንግሥት ባለሥልጣናት እስከ ወረዳ ያሉ የኢህአዴግ ካድሬዎች አለአንዳች እፍረት እኛን ኢትዮጵያውያን ሙስሊሞችን ስለ ሱፊያ እና ሰለፊያ ሊያስተምሩን ይገዳደራሉ፡፡ ካድሬ ጋዜጠኞችና የፌደራል ፖሊስም በመግለጫዎቻቸው፣ “ታላቁ መሪ” የተጠነቀቁትን ያህል እንኳ ሳይጠነቀቁ፣ “የወሃቢያ/ሰለፊያ ምንደኞች” እያሉ በአደባባይ አፋቸውን ይከፍቱብናል፡፡ ከቶውኑ እነዚህ ስያሜዎች ዊኪሊክስ ይፋ ካደረጋቸው የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ምሥጢራዊ ሰነዶች የተለቃቀሙ አይደሉምን?! ለመጀመርያ ጊዜ ከሟቹ ጠቅላይ ሚኒስትር አንደበት የተሰሙት “ነባሩ” እና “አዲሱ እስልምና” የሚሉ ስያሜዎችስ ከወዴት ተቃረሙና ነው እኛን ለመወንጀል ዊኪሊክስ የሚጠቀሰው?! … እኛማ ዊኪሊክስን እናመሰግነዋለን! ምክንያቱም፣ የተመሰገነው ዊሊያም አሳንጅ የኢሕአዴግ መንግሥትን በሃይማኖት ጉዳይ ውስጥ ጣልቃ በመግባት፣ በህዝብ‑ሙስሊሙ ተቋም ላይ ሹማምንቱን እንደሚያስቀምጥ ነውና ያጋለጠልን! …
የዩናይትድ ስቴትስ መንግሥት “የሳዑዲ ባህላዊ ወረራ” ሲል የጠራውን ይህን መሰሉን ተግባር ለመቀናቀን የወሰደው ለኢስላማዊ ቅርሶችና ታሪካዊ እሴቶች ጥበቃ እገዛ የማድረግ ባህላዊ መርኃ‑ግብር የሚደገፍ ቢሆንም፣ የጉዳዩ ባለቤት የሆነውን ህዝበ‑ሙስሊም ባሳተፈ መልኩ የተካሄደ አይደለም፡፡ በዚህም ምክንያት፣ ኤምባሲው በህዝብ ካልተመረጠው የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት አመራር ጋር በመተባበር ያከናወናቸው የቅርስ ጥበቃና ተሃድሶ ተግባራት ብዙዎችን ከጀርባው ሌላ ዕኩይ ዓላማ ያዘለ ሳይሆን አይቀርም ወደሚል ጥርጣሬ ገፍቷቸዋል፡፡
የኢሕአዴግ መንግሥት፣ የቴልአቪቭ ዩኒቨርሲቲ መምህር የሆኑት ፕሮፌሰር ሐጋይ ኤርሊች፣ ከሌላ አንድ ምሁር ጋር በጣምራ የሠሩትን ጥናት፣ እንዲሁም ምናልባት የቀድሞው የዩናይትድ ስቴትስ አምባሳደር ዶ/ር ዴቪድ ሺን በተለያዩ አጋጣሚዎች የሰጧቸውን የግል አስተያየቶች ዋቢ በማድረግ ይመስላል፣ አለ ብሎ የሚያስበውን የወሃቢያ አክራሪነት ለመቋቋም የአህባሽ አስተምህሮን ወደ ኢትዮጵያ ማምጣትን እንደመፍትኄ አድርጎ ወስዶታል፡፡ መንግሥት ከወሃቢያ አስተምህሮ ሊመነጭ ይችላል ብሎ የሚያስበውን የ“አክራሪነት” ስጋት ለመቋቋም፣ ከላይ በተጠቀሱት ምሁራን “ለዘብተኛ” ተብሎ የተሞካሸውን ሊባኖስ‑ወለድ አስተምህሮ በህዝበ‑ሙስሊሙ ላይ ለመጫን የህዝበ‑ሙስሊሙን የጋራ ሃይማኖታዊ ተቋም (መጅሊስን) መሣሪያ ለማድረግ በመሻት በተቋሙ ላይ የአህባሽ አስተምህሮ ተከታዮችን ሾሟል፡፡ ይህ ከሆነ በኋላ፣ በ2003 መገባደጃ ላይ የኢሕአዴግ መንግሥት “አክራሪነትን መዋጋት” በሚል ምክንያት፣ በዋነኛነትም የወሃቢያ አስተምህሮን ዒላማ በማድረግ የወሰዳቸው እርምጃዎችና፣ ይበልጡንም በህዝበ‑ሙስሊሙ ላይ የአህባሽን አስተምህሮ ለመጫን የተደረገው ሙከራ ከላይ የተጠቀሰውን ጥርጣሬ በማጠናከር እነሆ ሁለት ዓመታት ሊደፍን ለተቃረበው የኢትዮጵያውያን ሙስሊሞች የተቃውሞ እንቅስቃሴ መነሻ ሆኗል፡፡ መንግሥት ይህን ድርጊት በመፈፀም ከጣሰው ሕገ‑መንግሥት ባሻገር የህዝበ‑ሙስሊሙን የጋራ ተቋም ለአንድ እንግዳ አስተምህሮ ተከታዮች አሳልፎ በመስጠት የወሰደው እርምጃ በአገራችን በአስተምህሮ ላይ የተመሠረተ ከመቼውም ጊዜ የበለጠ ውጥረት ከመፍጠር በቀር ምንም ያመጣው አዎንታዊ ውጤት የለም፡፡ …
ላለፉት ሁለት ዓመታት ኢትዮጵያውያን ሙስሊሞች አጥብቀው እየተቃወሙ ያሉት እነዚህን የተሳሳቱ የችግር አፈታት መንገዶች ነው፡፡ የእኛ ሁኖ ሳለ የእኛ ያልሆነው የእስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ይህን የተሳሳተ የችግር አፈታት ከማረም ይልቅ፣ የተሳሳተው አካሄድ ዋነኛ ተዋናይ በመሆኑ የኢትዮጵያውያን ሙስሊሞች የተቃውሞ እንቅስቃሴ በዋነኝነት ይህን ተቋም እውነተኛ የህዝበ ሙስሊሙ ተቋም በማድረግ ላይ ለማተኮር ተገዷል፡፡ በኢትዮጵያ ላለፉት ሁለት ዓመታት እየተካሄደ በሚገኘው የህዝበ‑ሙስሊሙ ሰላማዊ ትግል የተነሱት ቁልፍ ጥያቄዎች በግልፅ የሚያመለክቱትም ይህንኑ ሐቅ ነው፡፡ ሰላማዊ ትግሉ በጠራ ግንዛቤና ግብ ላይ የተመሠረተ፣ በመላው ኢትዮጵያውያን ሙስሊሞች ሁለንተናዊ ተሳትፎ የሚካሄድ መሆኑ ይታወቃል፡፡ ይህ እንቅስቃሴ በአገራችን ሕገ‑መንግሥት በሠፈሩት የሃይማኖት ነፃነት ድንጋጌዎች ላይ እየተቃጡ ያሉ የመንግሥት ጥሰቶች እንዲቆሙ በግልፅ የሚጠይቅ እንጂ፣ ከቶውንም በሌላ እምነት ተከታይ ኢትዮጵያውያን ወገኖቻችን ላይ ዕኩይ ነገር ያለመና የተለመ አይደለም፡፡ ነገር ግን፣ ይህንን ህዝባዊ፣ ሕጋዊ እና ፍትኃዊ ጥያቄ በአግባቡ መመለስ ብልህነት መሆኑን ያልተረዳው የኢሕአዴግ መንግሥት፣ የህዝበ‑ሙስሊሙን ጥያቄዎች ላለመመለስ በወሰደው፣ በእኛ እምነት ፍፁም የተሳሳተ ፖለቲካዊ ውሳኔ ምክንያት፣ የፕሮፖጋንዳ አውታሮችን በመጠቀም ጉዳዩን ወዳልተፈለገ እና አደገኛ ወደሆነ አቅጣጫ እየለጠጠው ይገኛል፡፡ ከእነዚህ አደገኛ አካሄዶች ውስጥ አንዱና ዋነኛው በአገራችን ለረዥም ዘመናት በሰላምና በፍቅር አብሮ የመኖር እሴትን ባጎለበቱት የእስልምና እና የክርስትና ተከታይ ህዝቦች መካከል የእርስ በርስ ጥርጣሬና ግጭትን የመፍጠር ዕኩይ ስትራቴጂው ተጠቃሽ ነው፡፡
በኢትዮጵያ ዲያስፖራ የራዲዮ ጣቢያዎች ዊኪሊክስን ዋቢ በማድረግ የቀረቡት ዝግጅቶች ይህንን ዕኩይ ዓላማ ከመመገብ ውጪ ለኢትዮጵያ ህዝቦች በሰላም እና በፍቅር መኖር የሚያበረክቱት አንዳችም አዎንታዊ አስተዋጽዖ ይኖራል ብለን አናምንም፡፡ በሰነዶቹ ላይ የተጠቀሱትን የአሜሪካ መንግሥት ፖለቲካዊ ምሥጢራት ልክ ሙስሊም ኢትዮጵያውያን ከክርስትያን ወገኖቻቸው የደበቁት ምሥጢር አስመስሎ ለማቅረብ መሞከር እጅግ በጣም አሳፋሪ ነው፡፡ ከዚህ በላቀ የሚያሳዝነው ግን በዚሁ የራዲዮ ዝግጅት ጥቅም ላይ የዋሉት ምንጫቸው የማይታወቅ የድምፅ ግብዓቶች ናቸው፡፡ ከዓመታት በፊት በውሱን አካባቢዎች ከተከሰቱ ግጭቶች ውስጥ ስሜት ኮርኳሪ ድምፆችን እንደ በግብዓትነት ተጠቅሞ የሰዎችን ስሜት መኮርኮርም፣ ለአገር ሰላም ተቆርቋሪነትን ያሳያል ብለን አናምንም፡፡
ውድ የኢትዮጵያ ዳያስፖራ ራዲዮ “ጋዜጠኞች” እና የኢሕአዴግ የፕሮፖጋንዳ ድረ‑ገፆች ሆይ! ስለምን ተወናብዳችሁ የኢትዮጵያ ህዝብን ለማወናበድ ትሟሟታላችሁ?! እውን ተወናብዶ ህዝብን በማወናበድ አገር ይቀናል ብላችሁ ታስባላችሁን?! … እውነት እንላችኋለን፣ የምትጓዙበት መንገድ ደግ አይደለም፡፡ ግዴላችሁም አድምጡን፣ … እንደምናየው ደግ ነገርን አላለማችሁም፡፡ … ከመጎራበትም በላይ አንድ ግርግዳ ተጋርተው ለአያሌ ዓመታት በሰላምና በፍቅር በኖሩ ህዝቦች መካከል የጥላቻና የቁርሾ እሳትን ለመጫር የምትተጉት ከቶ ለዚህች አገር ምን ብትመኙላት እንደሆነ ሊገባን አልቻለም፡፡… እመኑን፣ ፍፁም በተሳሳተ መንገድ ላይ እየሄዳችሁ ነው፡፡ ግዴላችሁም ይህንን የኢትዮጵያውያን ሙስሊሞች ግሣፄ ከልቦናችሁ ሁናችሁ አድምጡት፡፡ … ወደ አቅላችሁ ብትመለሱ መልካም ነው፡፡ … ወደ አቅላችሁ ተመለሱና እንደማመጥ፡፡ … በሰላም መብታችንን በጠየቅን እየደረሰብን ያለው መገፋት ፈጽሞ ለርካሽ ፕሮፖጋንዳ ተንበርክከን የያዝነውን ሐቅ እንድንለቅ አያደርገንም፡፡ ይህንን ብታውቁት መልካም ነው፡፡ … ከእኛ ይልቅ እናንተ ፅንፍ ሄዳችኋል፡፡ … ግዴለም ዓይኖቻችሁን ክፈቱ፡፡
መልዕክታችንን ከፕሬዚደንት ኦባማ የካይሮ ንግግር በመጥቀስ እንደምድመው፡‑
“የግንኙነታችን ውል በልዩነቶቻችን ላይ እስከተመሠረተ ድረስ፣ ከሰላም ይልቅ ጥላቻን ለሚዘሩት፣ እንዲሁም መላ ሕዝቦቻችን ፍትኅና ብልጽግናን ያገኙ ዘንድ አስፈላጊ የሆነውን የትብብር መንፈስ ከማጎልበት ይልቅ የግጭትን ጎዳና መጥረግ ለሚሹት (ጽንፈኞች) ሁነኛ አቅም እንፈጥርላቸዋለን (የልብ ልብ እንሰጣቸዋለን)፡፡ እንዲህ ዓይነቱ የጥርጣሬና የቅራኔ ዑደት ማብቃት አለበት፡፡”

Thursday, August 29, 2013

የዱርየው ወያኔ መንግሥት የውሸት አምራች ፋብሪካዎች ይዘጉ


August 28, 2013
ተሾመ ደባለቄ
‘የሌባ ዓይነ ደረቅ መልሶ ልብ ያድርቅ’ ሲል የሀገሬ ሰው ሀገር ያወቀውን ፀሐይ የሞቀውን ሌባ ጨዋ ለማስመሰል የሚያጋጋው ውሸት ሲያሰለች ነው። እንደዚሁም መንግሥት ነኝ ተባዩ ወያኔም የውሸት ጋጋታው ሰውን አሰልችቶት እውነትም ቢናገር እነኳን የሚያምነው አጥቶ ሙጥኝ የያዛቸው መዋቅሮች ‘ውሸታም’’ ና  ‘ሌባ’ የሚል ስም አትረፈዋል።
ውርደት ያተረፈው ወያኔ የውሸት ጋጋታው አልበቃ ብሎት ለምን እውነት ተነገረ ብሎ ድርጅት መዘጋት ባልደረቦችን ማሳደድ፣ ማሰርና  እስከመግደል ደረጃ ደርሷል። በራሱ ውሸት ያበደው ወያኔ በአካባቢው ከሚያጎበድዱለት ጉጅሌዎቹ መሃል አብደሃል በሙስና ተዘፍዝፈሃል የሚለው ጠፍቶ እንደመሸበት ሰካራም ቤቱ ጠፍቶት በየሰዉ ቤት እያንኳኳ በራሱ ውሸት ተሸብሮ ህዘብን ማሸበሩን ቀጥሎበታል።
በመሰረታዊ ውሸት ላይ የተመሰረተው ወያኔ ‘ድንጋዩ ዳቦ ነው’ ብላችሁ ተቀበሉ እያለ መከራውን ሲያይ አዝለውት የሚዞሩት ጉጅሌዎቹ የውሸቱ ሸክም በዝቶባቸው  ሲዘላበዱና  በህዘብ መሳለቂያ ሲሆኑ ማየት ያሳፍራልም ያሳዝናል።
በዕውነቱ ውሸቱ በዝቶ የራሱ ነፍስ ፈጥሮ ወያኔን ማስተዳደር ከጀመረ ሰንብቷል ማለት ሀሰት አይሆንም። ይህ ከመሰረቱ በውሸት የተገነባው መንግስት ነኝ ባዩ ቡድን ወደሃላ መመለስ ስለማይችል የባሰ እያበደ ይሄዳል አንጂ እውነትን ለመቀበል ችሎታም አቅምም ሊኖረው አይቻልም። ስለሆነም እራሱን ወጥመድ ውስጥ አግብቶ ለማምለጥ ሲፈራገጥ ወገን እያቆሰለና አገር አያደማ መሆኑ ሊያስገርመን አይገባም።
ሆዳቸውን በውሸት የሞሉት ጉጅሌዎቹም ቢሆኑ ሆድን ከእውነት መርጠው እየቃዡ ምላሰቸው ተቆላልፋል። እውነት መናገርም የሚያጎርሳቸውን እጅ መንከስ ስለሆነባቸው እውነት የሚናገረውን መናከስ የሚረዳቸው መስሏቸው ሲዘላብዱ በህዘብና በሀገር ሲያፌዙ ይገኛሉ።
የቸገረው እርጉዝ ያገባል እንደሚባለው ቀንደኛው የውሸት መሪ ካለፈ ጀምሮ ውሸቱን ማስተዳደር አቅቷቸው ያዙኝ ልቀቁኝ እያሉ ሲዘባርቁ ለተመለከታቸው አብደው ሊያሳብዱ የተነሱ እንደሆኑ ግልጽ ነው። በእርግጥኝነት ሊባል የሚቻለው እብድ ማበዱን ካላመነ ጤነኛ ነኝ ብሎ እራሱን ስለሚያሳምን በእብዶች መሀል አንድ ጤነኛ ቢኖር እንኳን እንደ እብድ ስለሚቆጠር ያበዱትን ባልደረቦቹን ሊረዳቸው አይችልም።
የብዙሃን መገናኛ ላይ ያሰፈሰፉት ካድሬዎችን ብናስተውል የወያኔ ውሸት የራሱን ነፍስ እንዳላው ያረጋግጥልናል። እነዚህ የብዙሃን መገናኛ ተባዮች የውሸት ፋቢሪካ ሆነው በሶስት ፓኬጅ እያሸጉ ውሸትን ሊሸጡ ሲሯሯጡ ይታያሉ።
አንደኛው ፋብሪካ የውሸቱ ጥሬ ዘር የሚያመርተው በወያኔ የሚተዳደሩት መዋቅሮች ሲሆን የውሸት ምሶሶና በምንጭነት ፊት ቀዳሚ ሲሆን የህዋዓት ዋና መሳሪያ ነው። ሆኖም መንግሥት ነኝ የሚለው ወያኔ ስለተቆጣጠራቸው የሚያምናቸው አጥተው ወንዝ እንደሚያከራትተው ግንድ ይወዛወዛሉ።
woyane propaganda machineበሁለተኛ ደረጃ ያሉት የውሽት ፋብሪካዎች ወያኔ በካድሬዎቹ ያደራጃቸው መዋቅሮችና የብዙሃን መገናኛዎች (በተለይም በስደት ላይ ያለውን ወገን ለማወናበድ) የተዋቀሩ ናቸው። እነኝህ መዋቅሮች በወያኔ ጥሬ ወሸትና ገንዘብ የሚታገዙ ስለሆኑ አላማችው በግል ስም ወያኔ በመንግሥት ስም መሸጥ ያቃተውን ውሸት ዳግም ማሸግና መሸጥ ነው። እነዚህ ግለሰቦች ወያኔ ከመጣ ጀምሮ ማንነታቸው የማይታወቅ (ጎሬላዎች) ናቸው። ከተጋለጡት መሃል የአይጋ-ፎረም ባለቤት ኢሳያስ አፅብሃ  ከሳኖዜ ካሊፎሪኒያና የትግራይ-ነት ባለቤት ሚካኤል አባይ ከዴንቨር ኮለራዶ ይገኙበታል።
በሶስተኛ ደረጃ ያሉት የውሸት ፋብሪካዎች ደግሞ በነጻ ፕሬስ ስም የሚነግዱ መዋቅሮች ሲሆኑ እነሱም በሁለት ይከፈላሉ። አንዱ በወያኔና ባልደረቦቹ የሚተዳደሩ የውስጥ ሚስጥረና ድጋፍ ያለቸውና ዜጋ ለማወናበድ የተደራጁ የብዙሃን መገናኛ መዋቕሮች ናቸው። በሁለተኛ ደረጃ ደግሞ በተቃዋሚ ስም የተደራጁ አስመሳይ መዋቅሮች ናቸው። የሁለቱም አላማ አንድ ቢሆንም የውሸትን ማሸግና መሸጥ መንገዳቸው ይለያያል። ነገር ግን ሁለትም የወያኔን ሥርዓት በተወሰነ ደረጃ ይገስጻሉ ግን አላማቸው ወያኔን ማቆየት ስለሆነ መሰረታዊ ጉዳዮች ላይ እነዳይነኩ የታዘዙ ይመስላሉ። ሁሉቱም ከውጭ ሚዲያ የመጣን ወያኔን የሚያሞግስ ዜና አያመልጣቸውም ወይን ይፈጥራሉ። ሁለቱም ህዘብ ላይ የሚደርሰውን ግፍና ዘረፋ  ለመሸፈንና ለማደናገር ዘመቻ ላይ የተሰማሩ ናቸው። ሁሉቱም በጋዜጣ ስም አሰመስለው የፐሮፖጋነዳ  ሥራ ለመስራት ውስጥ ለውስጥ የተደራጁ የሥርዓቱ  ጉጅሌዎች ናቸው።
በውሸት ላይ የተሰማሩት የወያኔ ባልደረባና አስመሳይ ጋዜጠኞች ሥራዓቱ እየፈራረሰ ሲመጣ የሚያደርጉት ስለጠፋባቸው ወያኔን ለማዳን ያላቸው ብቻ ምርጫ የእስላም አሸባሪ መጣባችሁ እያሉ ማስፈፈራራት አዲሱ ሞያቸው ሆኗል። እሱንም ጉዳይ በተለያየ የውሸት ማቀነባበር መንገድ እያዘጋጁ ህዘብን በማተራመስና ለወያኔ ጊዜ ሊገዙለት እየጣሩ ነው።
ለምሳሌ ቀንደኛዎቹ የወያኔ የዜና መዋቅሮች የውሸት ቲያትር እያሰሩ ሲያሰራጩ በግል የዜና መዋቀር ስም የሚቀሳቀሱት ደግሞ ቲያትሩን እውነት ለማስመሰል የውጭ አከራሪዎችን ዜና በማነፈስ ህዘብን ቢያንስ እንዲጠራጠር አልያም እንዲያምን ይጥራሉ። ከዚህ በፊትም በአማራው ህብረተሰብ ላይ ያወረዱበት የውሸት ዘመቻ ስኪ ሆነ ብለው ስለሚያምኑ በእስልም ተከታዮች ወገኖቻችን ላይ እየመከሩት መሆኑ በግልጽ ይታያል።
ወገንም የነፃ ብዙሃን መገናኛዎችም የፖሎቲካና የሲቪክ መዋቅሮችን እነኚህን የውሸት ፋበሪካዎችንና የሚያንቀሳቅሷቸውን የውሸት መልክተኞች ማወቅ ማጋለጥና ከዛም አልፎም ማዘጋትና ተጠያቂ ማድርግ ግድ ይላል።
ትግሉ ማንንም ግለሰብንና ቡድን የውሸት ፋበሪካ ሰለባ እንዳይሆን የመከታተልና የመቅታት ዋናው ስራው መሆን ይኖርበታል። የወያኔ ሥርዓት እየገማ በመጣ ቁጥር ባልደረቦቹ እያባሱ መግማታቸው አይቀሬ ስለሆነ እያናዳንዱ ዜጋ እነኝህን የውሸት መልክተኞች መከታተል ሀላፊነት አለበት። የውሸት ፋብሪካ መዘጋትና ሥራ አስኪያጂዎች መቅጣት የዲሞክራሲ ትግል ዋናው ምሶሶ ስለሆነ ፋብሪካዎቹም ሆነ ሥራአስኪያጆቹ ዕውነት ያመርታሉ ማለት የህልም እነጀራና ሞኝነት ነው።
የኢትኦጵያ ሳተላይት ቴሌቪዥን (ኢሳት) ከመጣ ጀምሮ እንቅልፍ የነሳቸው የወያኔ ካደሬዎችና ተጠቃሚዎች የገዢውን ቡድን ውሸት እያሰራጩ ኢሳትን  የሚያጋልጠውን እውነት ሊነኩት አቅቷቸው አይናቸውን ጨፍነው ጆሯቸውን ደፍነው ቅዠት ውስጥ እንዳሉ እራሳቸው ይመሰክራሉ።  ኢሳት አንዱ ትልቁ ሥራው እንኝህን የወያኔን ውሸት ፋብሪካና ቸርቻሪ ባለቤቶችን ለህዘብ ማጋለጥና ማንነታቸውን ህዝብ እንዲያውቃቸው ማድረግ ነው።
የኢትዮጵያ ህዝብ ነፃነቱን በቶሎ የሚጎናፀፈውና የወደፊት ሰላምና ብልጽግና የሚያገኘው የውሸት ፋብሪካዎች ሲዘጉና የእውነት ፋብሪካዎች ሲስፋፉ ነው።  ይህ መሰረታዊ መፍቴህ የውሸት ፋበሪካ ባለቤቶችን እያሳበዳቸው ጨርቃቸውን ጥለው እየሮጡ እነዳሉ ግልጽ እየሆኑ መጥተዋል። ሆኖም በቂ ትኩረት ተሰጥቶት ስላልተሰራ ተደብቀው ውሸትን ማምረትና መቸርቸር ሥራቸውን ቀጥለዋል።  በድርጅት ከመስራት በግለሰብ መሥራት የባህል ድክመት ብዙዎቹን የነፃ ሚዲያዎችን ያዳከመና የውሸት ፋብሪካዎችን እድል ከፍቶላቸዋል ማለት ይቻላል።
የውሸት ፋብሪካዎችን ለማዘጋት ባለቤቶቹንም ለመቅጣት እንዘጋጅ እንደራጅ
ድል ለኢትዮጵያ ህዘብ

የሕወሐት ባለስልጣናት የአሜሪካ ቆይታ፤ የከዱ አሉ


August 29, 2013
ከኢየሩሳሌም አርአያ
በአባይ ወልዱ የሚመራውና ሰባት ከፍተኛ የሕወሐት ባለስልጣናት የተካተቱበት ቡድን በአሜሪካ አራት ከተሞች ባካሄደው ስብሰባ በተለይ በላስቬጋስ ጠንካራ ተቃውሞ እንደገጠመው በስፍራው የተገኙ ምንጮች አስታወቁ። ቡድኑ በዋሽንግተን ኢትዮጲያ ኤምባሲ በጀመረውና በመቀጠል በላስቬጋስ፣ ሲያትልና ካሊፎርኒያ ከተሞች ባካሄደው ስብሰባ “አላማ” አድርጎ የያዛቸው ጉዳዮች እንደነበሩ የጠቆሙት ምንጮች፣ እነሱም፥ “የመለስ ፋውንዴሽን፣ የአባይ ግድብና የ40/60 የቤቶች ግንባታ.” ሲሆኑ፣ ለነዚህ ማስፈፀሚያ “ገንዘብ አዋጡ” የሚለው ዋናው ግብ እንደነበር አስረድተዋል። በተለይ ደግሞ « በትግራይ ተወላጁ ዘንድ ሕወሐት የለም፣ ተከፋፍሏል፣ ተዳክሟል፣ ፓርቲው ሰው የለውም፤» የሚለውን እራሱ ቡድኑ በማንሳት ለገዛ ጥያቄው መልስ ሲሰጥ « ሕወሐት አሁንም ሃይል አለው፤ አልተዳከመም» በማለት አድራጊ- ፈጣሪ በመሆን ስልጣኑን በበላይነት ተቆጣጥሮ እንደያዘና ቡድኑ የመጣውም “አይዟችሁ” ለማለት እንደሆነ መገለፁን በቅርብ የተከታተሉት ምንጮች አስታውቀዋል። ቡድኑ በተጨማሪም ፥ « ልማት አልምተናል፤ ትግራይ እየለማ ነው፤ ህዝቡን ተጠቃሚ እያደረገነው ነው» ከማለቱ ባሻገር « በትግራይ ተወላጁ ላይ አደጋ ተደቅኗል፤ የሙስሊሙ፣ የትምክህተኞችና የሽብርተኞች አደገኛ እንቅስቃሴ እያንዣበበ መሆኑን፣…የተደቀነብህን አደጋ ከጎናችን ሆነህ ተከላከል፤ ያለበለዚያ ግን ሊያጠፉህ ነው፤» ሲሉ መናገራቸውን የገለፁት ምንጮች አክለውም፣ « አባላት የሆናችሁ ተወደደም ተጠላ መሬትና መኖሪያ ቤት እንሰጣችኋለን፤ ለዚህም ከእኛ ጎን መሰለፍ አለባችሁ» በማለት ሊሸነግሉ መሞከራቸውን ጠቁመዋል።
ከዋሽንግተን ስብሰባ (ለሁለት ተከፍሎ ነው የተካሄደው) በኋላ ወደ ሶስቱ ከተሞች ተከፋፍለው እንደሄዱ ሲታወቅ፥ ሲያትል አቶ ብርሃነ ማረት፣ እንዲሁም ላስቬስጋስ አባይ ወልዱና ተክለወይኒ አሰፋ መሄዳቸው ታውቋል። በተለይ በላስቬጋስ ጠንካራ ተቃውሞ የገጠማቸው እነአባይ ስብሰባው ከቀኑ 2፡00 ሰዓት ይጀመራል ተብሎ ከአራት ሰዓት በኋላ ዘግይቶ አመሻሽ ላይ መጀመሩን ምንጮች ገልፀዋል። ስብሰባው ሲጀመር ከላይ የተገለፁትን ጉዳዮች ያደመጠው ተሰብሳቢ ተከታዮቹን ጥያቄ አቀረበ፤ « ዴሞክራሲ አለ ትላላችሁ፣ ነገር ግን ዴሞክራሲ የለም፤ በሃሳብ የሚቃወማችሁን ታስራላችሁ፣ ታንገላታላችሁ፣ የሰብአዊ መብት ረገጣ ታካሂዳላችሁ፤ ከእናንተ የተለየ ሃሳብ ያለውን ትፈራላችሁ፤ ለምንድነው ይህን ሁሉ የምታደርጉት?….በማ.ረ.ት.(ማህበር ረድኤት ትግራይ) በትግራይ ሕዝብ ስም የምትሰበስቡትን ገንዘብ ለአራጣ ብድር እና ለፖለቲካ መጠቀሚያ በመሳሪያነት እያዋላችሁት ነው። ለምን?….ትእምት (ኤፈርት) ማነው ባለቤቱ?..በማን ነው የሚመራው?..ማነው የሚቆጣጠረው?..ለመሆኑ ኦዲት ተደርጎ ያውቃል ወይ?..እነማናቸው እየተጠቀሙበት ያለው?» የሚሉት ዋና ዋናዎቹ ጥያቄዎች እንደነበሩ ምንጮቹ የጠቆሙ ሲሆን፣ አባይ ወልዱ « እኔ አልመልስም፣ ተ/ወይኒ መልስ ይስጥበት» ቢሉም ነገር ግን ግልፅና አግባብ ያለው ምላሽ ከመስጠት ይልቅ ወደ ማመናጨቅና ቁጣ ያመሩት ተ/ወይኒ በዚህ ድርጊታቸው በርካታ ተሰብሳቢዎችን እንዳሳዘኑ አስረድተዋል። በዚህ የተበሳጨው ተሰብሳቢ « ጥያቄያችን አልተመለሰም» በማለቱና ሁከትና ያለመደማመጥ በማየሉ ስብሰባው እንዲቋረጥ መደረጉን የጠቆሙት ምንጮች፣ የጥያቄና ተቃውሞው መብዛት ያስደነገጣቸው ባለስልጣናቱ የመረጡት ማምለጫ በላስቬጋስ ተወካያቸው በሆነውና መድረክ ሲመራ በነበረው አቶ ተወልደ በኩል፥ « አዳራሹን የተከራየንበት ሰአት አብቅቷል፤ ስለዚህም ስብሰባው አብቅቷል » በማለት በአስቂኝ ሰበብ መቋረጡን አያይዘው ገልፀዋል። እነአባይ ከአዳራሹ ሲወጡ ቀድሞ ውጭ ሆኖ ይጠብቃቸው በነበረው ተሰብሳቢ ውግዘትና ስድብ እንደደረሰባቸው ያስታወቁት ምንጮች « ሌባ..ሌባ…ሙሰኞች..» የሚሉ ተቃውሞዎች ጎላ ብለው እንደተሰሙ አመልክተዋል።
ስብሰባዎቹን የታዘቡ ወገኖች በሰጡት አስተያየት እንዲህ ብለዋል፤ « በአንድ በኩል ልማት እያካሄድን ነው፤ እያሉና ገንዘብ እየጠየቁ በሌላ በኩል “ትግራዋይ አደጋ ተደቅኖብሃል፣ ከጎናችን ሆነህ ተከላከል፤” ማለት እርስ በርሱ የሚጋጭና ድጋፍ የማግኛ የፖለቲካ የፖለቲካ ቁማር ነው። ያልተጠየቁትን የፓርቲውን ህልውና (ስለ ሕወሐት) አንስቶ መነገሩም አስገራሚና አጠያያቂ ነው።» ሲሉ ትዝብታቸውን የጀመሩት እነዚህ ወገኖች በማያያዝም፥ « እነዚህ ሰባት ባለስልጣናት ወደ አሜሪካ የመጡት ከነዘመዶቻቸው፣ ጋሻ ጃግሬዎቻቸው ሲሆን፣ ባለስልጣናቱ የመንግስት ወኪሎች እንደመሆናቸው – በማን ገንዝብ ነው የሚንቀሳቀሱት?..የሚለው መጠየቅ አለበት። በሕዝብ ገንዝብ እየተንፈላሰሱ እንደሆነ ግልፅ ነው። የትግራይ ተወላጁን ብቻ ለይተው ስብሰባ የሚጠሩት ለምንድነው?…በእርግጥ ስላሰቡለት ነው?…የሚሉት ሲፈተሹ .መልሱ በጭራሽ አይደለም ነው። አላማቸውና ትኩረት የሰጡት የትግራይ ተወላጁን እየተንከባከቡት እንደሆነና ተጠቃሚ መሆኑን ለማሳየት በመፈለግ፣ እግረ-መንገዳቸውን ከቀሪው ኢትዮጲያዊ ወገኑ ጋር በመነጠል..ድጋፍ ለማግኘትና በውስጣቸው የተፈጠረውን ቀውስ በዚህ በኩል ቀዳዳውን ለመድፈን የሚደረግ የስልጣን እድሜ ማራዘሚያ ስልት ነው። ..ደግሞስ ሕወሐት “አጋር” ከሚላቸው ብ.አ.ዴ.ን፣ ኦ.ህ.ዴ.ድ.፣ ደቡብ ሕዝቦች ተለይቶ፣ በሕዝብ ገንዘብ ስብሰባ የሚጠራበትና ያሻውን የሚያደርግበት አግባብ ምንድነው?..የሚለው ከዚህ ጋር መታየት ያለብት ነው። ፖለቲካዊ ፍጆታና ማንአለብኝነት በፓርቲው በመነገሱ እንደሆነ ደግሞ ግልፅ ነው።» ብለዋል።
ይህ በእንዲህ እንዳለ፥ አሜሪካ ከመጡት ሰባት የሕወሐት ባለስልጣናት መካከል- ማለትም አባይ ወልዱ፣ ብርሃነ ኪ/ማሪያም፣ ተ/ወይኒ አሰፋና ዳንኤል አሰፋ በዋነኛነት ሲጠቀሱ፣ ከሰባቱ ሶስቱ ስብሰባውን ሳያካሂዱ ከቡድኑ ተገንጥለው በአሜሪካ መቅረታቸውን ምንጮች አረጋግጠዋል። ቤተሰቦቻቸውን ይዘው (ልጆቻቸውን ጭምር) በመምጣት አሜሪካ ጥገኝነት ጠይቀው መቅረትን የመረጡት ባለስልጣናት ውስጥ የሕወሐት ማ/ኮሚቴ አባላት እንዳሉ ያረጋገጡት ምንጮች በቅርቡ ዝርዝሩን ይፋ እንደሚያደርጉ አስታውቀዋል።

Tuesday, August 27, 2013

በአዕምሮ ሁከት የተለከፈችው እህት በጅዳ! በትዞራለች… ትዞራለች… ሲደክማት ታርፈና አሁንም ትዞራለች!


August 26, 2013
ነቢዩ ሲራክ
አንድ ወዳጀ መሃመድያ ተብሎ በሚጠራው የጅዳ ከፍል ከኢትዮጵያ አለም አቀፍ ትምህር ቤት አካባቢ ይህችን በፎቶው ላይ የምታዩዋትን እህት አግኝቶ ሊያነጋግራት ቢሞክርም ፈቃደኛ አልነበረችም። ከየት ነው የመጣሽ ? ስትባል” ከመቀለ ” ከማለት ባለፈ ስሟንና የሆነችውን አትናገርም ። ብዙ ሊያግባባት ሞክሮ ያልተሳካለት ይህ ወዳጀ ይህች እህት ያደፈና የተቀደደ ጥቁር “አባያ” ለብሳና መናኛ ነጠላ ጫማ የተጫማችው እህት የአዕምሮ ሁከት እንዳለባት የተረዳው ብዙ ለማነጋገር ሞክሮ በሰጠችው አንዳንድ ምላሽ እንደሆነ ገልጾልኛል! ልጁን ትምህርት ቤት ሊያስመዘግብ በሔደበት አጋጣሚ በጠራራው ሜዳ ስትንከራተት በማየቱና ምንም መርዳት ባለመቻሉ ያዘነው ወዳጀን መረጃ ይዠ የጅዳን ቆንስል ሃላፊዎች ስልክ በመደዎል ይህችን እህት በመጠለያው አምጥተው ሌላው ቢቀር ካሉት የአዕምሮ በሽተኞች ጋር ቀላቅለው ከመኪና እና ከመሳሰሉት አደጋዎች አንዳትጋለጥ ይሰበስቧት ዘንድ ለማሳወቅ ያደረግኩት ሙከራ አልተሳካም!Ethiopian in Saudi Arabia
አንድ ሌላ ወዳጀ ከትናነት በስቲያ የዚህችን እህት አሁን ድረስ በአካባቢው መኖርና ዝም ብላ እንደምትዞር ነገረኝና ወዳለችበት አካባቢ ሔጀ በአካል ለማነጋገር ሞክሬ ነበር ። በጠራራው ጸሃይ የውሃ ፕላስቲክ ባንድ እጇ በሌላ እጇ ፊስታል አንጠልጥላ እየሳቀች እና እየተኮሳተረች ክው ክው እያለች የምትራመደው እህት አገኘኋት። ብዙ ከተከትልኳት በኋላ አረፍ ስትል ጠብቄ አማርኛ ትችያለሸ ? አልኳት “ግደፈኒ” አለችኝ ፊቷን ዘወር እያደረገች! ለማግባባትና ለማቅረብ ሞከርኩ ፣ ልታሰቀርበኝ አልቻለችም! ብዙ ተከተልኳት! … ትዞራለች …ትዞራለች …ሲደክማት ታርፈና አሁንም ትዞራለች ! በቃ ! እንዲህ ሆናለች …
ዛሬም እዚያው አካባቢ እየዞረች እንደምትገኝ ወደ ትምህርት ቤት ለጉዳዩ የሔደ ወንድም አግኝቷት በስልክ ገልጾልኛል። ስትንከራተት አይቶ ሊረዳት የፈለገው ይህ ወንድም እሱም ሆነ ያየውን የዚህች እህት አበሳ ያሳያቸው የትምህርት ቤቱ ሴት ኢትዮጵያውያን መምህራን ተከትለው ሊያነጋግሯትና ሊረዷት ቢፈልጉም ፈቃደኛ ባለመሆኗ ምንም ማድረግ እንዳልቻለ እያዘን ካነሳው ፎቶ ጭምር ልኮልኛል! ዛሬም ይህን መረጃ ለማቀበል ወደ ጅዳ ቆንስል ሃላፊ ወደ ቆንስል ጀኔራል ዘነበ ከበደ እና ቆንስል ሙንትሃ ስልክ ደውየ የነበረ ቢሆንም ሊመልሱልኝ ግን አልቻሉም! ይህ በእንዲህ እንዳለ በተፈናቃይ ሰራተኞች ዙሪያ ጥናት ለማድረግ በአንባሳደር ውብሸት የተመራ ቡድን ዛሬም በጅዳ ከቆንስል ሃላፊዎች ጋር በመምከር ላይ መሆኑን ታውቋል።
ቸር ያሰማን !
ነቢዩ ሲራክ

Monday, August 26, 2013

ሰንደቅ አላማውን ያዋረደው ማን ነው?


August 25, 2013
ጌታቸው ሺፈራው
ለዚህ ጽሁፍ መነሻ የሆነኝ ‹‹መንግስት በእምነታችን ጣልቃ እየገባ ነው!›› በሚል ከአንድ አመት በላይ እየተቃወሙ የቀጠሉት የእስልምና እምነት ተከታዮች ሀምሌ 19/2005 ዓ/ም ባደረጉት ሰላማዊ ሰልፍ ኢህአዴግ ‹‹ሰልፈኞቹ የሰንደቅ አላማውን ክብር አዋርደዋል?›› የሚል ክስ ማቅረቡ ነው፡፡ እኔ በበኩሌ የተበጣጠሰውን ሰንደቅ አላማው የያዙት ሰልፈኞቹን የሚኮንን መንግስት ቅጥረኞችም ይሁን ሰልፈኞቹ ትክክል ነው ብዬ አላምንም፡፡ ምንም እንኳ ህግ የማስከበር ሀላፊነት የነበረበት ቢሆንም ኢህአዴግ ጉዳዩን ያነሳው በእርግጥም በሰንደቅ አላማ ክብር ስለሚያምን አይደለም፡፡ የዚህ ጽሁፍ አላማም ሀምሌ 19/2005 ዓ/ም የተፈጠረው ስህተትን ማስተባበል አሊያም መክሰስ ሳይሆን በተፈጠረው ክስተት ‹‹ሌሎችን›› የሚከሰው ኢህአዴግ ራሱ ሰንደቅ አላማውን እያዋረደ መቀጠሉን  የተለያዩ ክስተቶችንና የራሴን ገጠመኝ በመቃኘት ማሳየት ነው፡፡Ethiopian national flag
ሰንደቅ አላማ የአንድ አገር ዋነኛ ምልክት በመሆን ያገለግላል፡፡ ለቅኝ ግዛት እጇን ያልሰጠችው የኢትዮጵያ ሰንደቅ አላማ ደግሞ ከዚህም በላይ ክብር አግኝቷል፡፡ በተለይ በጸረ ቅኝ ግዛት ዘመን አፍሪካውያንና በተለያዩ የዓለም ክፍሎች የሚገኙ ጭቁን ጥቁሮች የኢትዮጵያን ሰንደቅ አላማ የነጻነት አርማ አድርገው ተጠቅመውበታል፡፡ የአፍሪካ፣ የካሪቢያንና የደቡብ አሜሪካ አገራትም ይህን የነጻነት አርማ ቅርጽና አቀማመጡን ብቻ በመቀያየር ለአገራቸው መለያነት እየተጠቀሙበት ይገኛሉ፡፡ ከ6 ሚሊዮን በላይ ራስ ተፈሪያን ህዝቦችም የነጻዋን ኢትዮጵያ ሰንደቅ አላማ ከአምላክ የተላከ አንዳች ምልክት አድርገው እስከ ማምለክ ደርሰዋል፡፡ ይህም የኢትዮጵያን ሰንደቅ አላማ በዓለም ለበርካታ አገራትና ኢትዮጵያዊ ባልሆኑ ህዝቦች መለያነት ያገለገለ ብቸኛውና ተወዳጅ ሰንደቅ ያደርገዋል፡፡
በሌላ በኩል ይህ ዓለም አቀፍ ክብር ያለው ሰንደቅ አላማ በተለያዩ ጊዜያት አገር ውስጥ ክብሩ ተዋርዶ ተስተውሏል፡፡ የመጀመሪያው ለሰንደቁ ክብር መሰረት በሆነው አድዋ በኢትዮጵያውያን የተሸነፉት ፋሽስቶች ኢትዮጵያን ዳግመኛ ሲወሩ የፈጸሙት ነው፡፡ ጣሊያን ለአምስት አመት ኢትዮጵያ ውስጥ በነበረችበት ወቅት የኢትዮጵያ ሰንደቅ አላማ በሌሎች አፍሪካውያንና በተለያዩ የዓለም ክፍሎች በሚገኙ ጥቁሮች ዘንድ በስፋት በመለያነት ላይ የዋለ ቢሆንም ኢትዮጵያ ውስጥ ግን በጣሊያን ሰንደቅ አላማ ተቀይሯል፡፡ ይህ ከአንድ ‹‹ያልሰለጠነ›› በሚሉት ጥቁር ህዝብ ሽንፈትን ከተከናነበ የአውሮፓዊ ሀይል የሚጠበቅ ነው፡፡ ከዚህ ይልቅ የሚያሳዝነው ግን ጣሊያን ተባራ እንደገና ክብሩን ያገኘው ሰንደቅ በኢትዮጵያውያን ያውም የመንግስትን ስልጣን በያዘው ኢህአዴግ የደረሰበት ውርደት ነው፡፡ ለእኔ ሰንደቁን አውርደው የራሳቸውን ከሰቀሉት ጣሊያኖች በላይ ሰንደቁን ሰቅለው ‹‹ጨርቅ›› ያሉት የኢትዮጵያው አቶ መለስ ዜናዊና ኢህአዴግ ናቸው ሰንደቁን ያዋረዱት፡፡
ፋሽስት ከኢትዮጵያ ምድር ከወጣ 50 አመት በኋላ ስልጣን ላይ የወጣው ኢህአዴግ መሪ አቶ መለስ ዜናዊ ሰንደቁን ‹‹ጨርቅ›› ብለው ባዋረዱበት ወቅት እነ ጋና፣ ጊኒ፣ ማሊ ሌሎች ከ10 በላይ አገራት የእኛውን ሰንደቅ አላማ ወስደው ያደመቁበት ዘመን ነው፡፡ አሁንም ከእኛው ይልቅ ከእኛ የወሰዱት አገራት ሰንደቁን ትልቅ ክብር ሰጥተውታል፡፡ በወቅቱ አቶ መለስ ዜናዊ ይህን ክብረ ነክ ተግባር ሲፈጽሙ ከተቃዋሚዎች፣ ከነጻው ሚዲያ እንዲሁም ከህዝብ ውጭ ከፓርቲያቸው ምንም አይነት ግፊት አልተደረገባቸውም፡፡ በመሆኑም ለዚህ አሳፋሪ ተግባር እርሳቸውም ሆነ ፓርቲው ህዝብን ይቅርታ ሳይጠይቁ በዚሁ ሰንደቅ ስም ሲገዙ ቆይተዋል፡፡
ኢህአዴግ በ2001 ዓ/ም የሰንደቅ አላማ አዋጅን አውጥቶ ‹‹የሰንደቅ አላማ ቀን›› ማክበር ሲጀመር በርካቶች ‹‹ሰንደቁ ወድቆ ተነሳ!›› በማለት ኢህአዴግ ለሰንደቅ አላማው ክብር በመስጠት ከስህተቱ መማር እንደጀመረ እምነት ጥለው ነበር፡፡ ሆኖም ሰንደቅ አላማው አሁንም ክብር አልተሰጠውም፡፡ የሰንደቅ አላማ አዋጅም ሆነ በስሙ ‹‹የሚከበርለት በዓል›› ኢህአዴግ ሰንደቁን እንዳላዋረደ ለማሳየት እንጅ ክብሩን የሚገልጽበት አይደለም፡፡ ኢህአዴግና የቀድሞው መሪ ‹‹ጨርቅ›› ብለው ለጠሩት ሰንደቅ አላማ አዋጅ ሲያወጡም ሆነ ‹‹በዓል›› ሲያከብሩ ለቀደመው ጥፋታቸው ህዝብን ይቅርታ አልጠየቁም፡፡ የሰንደቅ አላማ አዋጅ ያወጣውና በዓል እያከበርኩ ነው የሚለው ኢህአዴግ አሁንም ቢሆን ለሰንደቁ የሚሰጠው ክብር የይስሙላህ ነው፡፡
ከመለስና ከሰንደቁ ማን ክብር አለው?
ሰንደቅ አላማውን ‹‹እራፊ›› ያሉት አቶ መለስ ከህዝብና ከተቃዋሚዎች ከደረሰባቸው ትችት ባለፈ በፓርቲያቸው ምንም አይነት ግፊት አለመደረጉ ኢህአዴግ ከሰንደቁ ይልቅ ስልጣን ሊነጥቁ፣ ሊሰጡ፣ ‹‹ሊያራግፉ›› አሊያም ሊያስሩ ለሚችሉት አቶ መለስ ክብር ሰጥቷል ማለት ነው፡፡ በእርግጥ በብሄር ስም የተደራጁት የኢህአዴግ አባል ፓርቲዎች ከአገሪቱ ሰንደቅ አላማ ይልቅ ለየክልሉ ‹‹ባንዲራ›› ክብር የሚሰጡ ናቸው፡ ለዚህ ደግሞ የካሪቢያንና ሌሎች የአፍሪካ አገራት የኢትዮጵያን የሰንደቅ አላማ ቀለማት ሲወስዱ አብዛኛዎቹ የኢህአዴግ አባል ፓርቲዎች ለክልሎቻቸው ከእኛዎቹ ቀለማት ይልቅ ቀይ ባህር፣ ሜዲትራኒያንና አትላንቲክን ተሸግረው የአረብና የምዕራባዊያንን የሰንደቅ አላማ ቀለማት መዋሳቸው ነው፡፡ የሰንደቅ አላማ አዋጅና በዓል መከበር ከተጀመረ በኋላም ቢሆን ኢህአዴግ እነዚህ ራሱ ያጸደቃቸውን ህጎች ጥሶ ከሰንደቅ አላማው የአቶ መለስን ክብር አስበልጧል፡፡ ጥቂት ክስተቶችን እንመልከት፡፡
በ2004 ዓ/ም መጋቢት አጋማሽ አካባቢ ሰንደቅ አላማውን ‹‹እራፊ›› ያሉት አቶ መለስ ከኬንያና ደቡብ ሱዳን ጋር እንደ ሰንደቁ ሁሉ ‹‹ሸቀጥ›› ብለው የሚያጣጥሉት ወደብ ላይ አንድ ስምምነት አድርገው ነበር፡፡ በዚህ የለሙ ወደብን በአማራጭ ወደብነት ለመጠቀም ባደረጉት ስምምነት ድሮም የማይወዱትን ሰንደቅ አላማ ገልብጠውት ታይተዋል፡፡ በአቶ መለስና ኢህአዴግ የበላይነት የጸደቀው የኢፌደሪ ህገ መንግስት በአንቀጽ 3(1) እንዲሁም በ2001 ዓ/ም የወጣው አዋጅ የኢትዮጵያ ሰንደቅ አላማ ቀለሞች አቀማመጥ ከላይ ወደ ታች አረንጓዴ፣ ቢጫና ቀይ መሆኑን ያስቀምጣል፡፡ በተለይ በሰንደቅ አላማው አዋጅ አንቀጽ 17 መሰረት ‹‹(ጠቅላይ ሚኒስትሩ ይቅርና) ማንኛውም ዜጋ ለሰንደቅ አላማው የሚገባውን ክብር የመስጠት ሀላፊነትና ግዴታ›› አለበት በሚል ደንግጓል፡፡ በአዋጁ አንቀጽ 23(6) ላይ ደግሞ የሰንደቅ አላማውን ቀለማት ቅደም ተከተል ሳይጠብቅ ማውለብለብ የተከለከለ መሆኑን ይደነግጋል፡፡ በአንቀጽ 24(1) ላይ ይህን ህግ የተላለፈ ግለሰብ ከ3000 ሺህ ብር መዋጮና እስከ አንድ አመት ጽኑ እስራት እንደሚፈረድበት በግልጽ አስቀምጧል፡፡ ኢህአዴግ በቅርቡ የሙስሊም ሰልፈኞቹን ‹‹ጥፋተኛ›› ብሎ የፈረጀው በዚህ አዋጅ ላይ ያሉትን ህጎች መዞ ነው፡፡ አቶ መለስ ላይ ግን ይህ ህግ አልሰራም፡፡
አቶ መለስ የገለበጡት አውቀው ነው በስህተት የሚል ጉንጭ አልፋ ክርክር ውስጥ መግባት አያስፈልግም፡፡ በህጉም መሰረትም ቢሆን አለማወቅ በራሱ ከጥፋተኝነት ሊያድን አይችልም፡፡ ዳግመኛ እንዲያውም በራሳቸው ትዕዛዝ የወጣውን አዋጅ ጥሰው ሰንደቁን ያዋረዱት አቶ መለስ ግን 3000 ብርና የአንድ አመት እስር ይቅርና ይቅርታ አልጠዩቁም፡፡ ኢህአዴግም እርሳቸውን ወክሎ ይቅርታ አይጠየቀም፡፡ እንዲያውም አቶ መለስ ሰንደቅ አላማውን መገልበጣቸው ስህተት መሆኑን የገለጹ ኢትዮጵያውያን ላይ ‹‹ምን አገባችሁ!›› ተብለው እርምጃ ተወስዶባቸዋል፡፡ ለዚህ ደግሞ እኔው ራሴ ቋሚ ምስክር ነኝ፡፡
በወቅቱ ለአቶ መለስ ተጠሪ በሆነ ‹‹ኢንሳ›› በተባለ መስሪያ ቤት ውስጥ ተቀጥሬ እሰራ ነበር፡፡ እንደ አንድ ኢትዮጵያዊ ዜጋ አቶ መለስ በፈጸሙት ነገር ተቃውሞ ማሰማት ነበረብኝና በፌስ ቡክ ገጼ ትክክል አለመሆኑን ፎቶውን አስደግፌ ሀሳቤን ገለጽኩ፡፡ ታዲያ ከሰንደቅ አላማው ይልቅ ለአቶ መለስ ክብር የሚሰጡት የመስሪያ ቤቱ አመራሮች (ኢህአዴጎች ናቸው) ጠቅላይ ሚኒስትሩ እስከሆኑ ድረስ ሰንደቅ አላማውን መዘቅዘቃቸው ስህተት መስሎ አይታያቸውም፡፡ በተቃራኒው እኔ ‹‹አቶ መለስ ለምን ሰንደቅ አላማውን ዘቀዘቁት?›› ብዩ መጠየቄን በህገ ወጥነት ፈረጁት፡፡ ሰንደቅ አላማውን ‹‹ጨርቅ›› ሲሉም ሆነ ሲዘቀዝቁ ምንም ያልተባሉት አቶ መለስ ላይ ጥያቄ በማንሳቴ ‹‹የጠቅላይ ሚኒስትሩን ክብር አዋርደሃል!›› በሚል ‹‹ወንጀል›› ተከስሼ ከመስሪያ ቤት ታገድኩ፡፡ ህገ መንግስቱም ሆነ አዋጁ ስለ ሰንደቅ አላማ ክብር ያስቀመጠውን ጠቅሼ መከራከሬ ‹‹በከፍተኛ ወንጀል›› ከመስሪያ ቤቱ ከመባረር አላዳነኝም፡፡
ከሟቹ መለስም ያነሰው ሰንደቅ አላማ
ለሰንደቅ አላማው ጥላቻ ያላቸው አቶ መለስ ብቻ ቢሆኑ ኖሮ አቶ መለስ ከሞቱ በኋላ ኢህአዴግ ለሰንደቅ አላማው ከድሮው የተለየ ክብር በሰጠ ነበር፡፡ ሰንደቅ አላማ ከተዘቀዘቀ ከወራት በኋላ በስልጣን ዘመናቸው ሰንደቅ አላማውን ሲያዋርዱ የኖሩትና በኢህአዴግ ዘንድም ከሰንደቅ አላማው በላይ የሚከበሩት አቶ መለስ ከዚህ ዓለም በሞት ይለያሉ፡፡ ከአቶ መለስ ሞት በኋላ ረዥም የሀዘን ቀን መታወጁ ይታወሳል፡፡ ለዚህ ሀዘን ሲባል ደግሞ አገራዊ ቀናትም ተራዝመዋል፡፡ አሊያም ተሰርዘዋል፡፡ በአዋጅ የተወሰነው የሰንደቅ አላማ ቀን ከተራዘሙት መካከል አንዱ ነው፡፡
በአዋጅ 654/2001 መሰረት የሰንደቅ አላማ በዓል በየ አመቱ መስከረም ሁለተኛ ሳምንት ላይ በአገር ደረጃ እንዲከበር ቢደነገግም ኢህአዴጎች ‹‹አይሞትም!›› ለሚሏቸው አቶ መለስ ሀዘን ሲባል ለጥቅምት ሶስተኛ ሳምንት (ሰኞ ጥቅምት 19) ተራዝሞ ‹‹ተከብሯል››፡፡ በዚህ ቀንም ቢሆን ከሰንደቅ አላማው ይልቅ ህወሓት ከተመሰረተበት ጊዜ ጀምሮ ያለው የአቶ መለስ 38 አመት ታሪክ በሚዘክር መልኩ ተከብሮ ውሏል፡፡ እናም ከሰንደቅ አላማው ይልቅ ተከብረው የዋሉት አቶ መለስ ነበሩ፡፡
በኢህአዴግና ሰንደቅ አላማው መካከል ያለውን ተቃርኖ ተከትሎ የሚመጣው መዘዝ ደግሞ እኔን አልለቀቀኝም፡፡ በወቅቱ ሰንደቅ አላማውን አዋርደው ምንም ያልተባሉትን አቶ መለስን ‹‹አዋርደሃል!›› በሚል ተባርሬ መሰናዘሪያ ጋዜጣ ላይ እየሰራሁ ነበር፡፡ በአቶ መለስ ሀዘን ምክንያት ተራዝሞ ሲወደሱበት ከዋሉት ‹‹የሰንደቅ አላማ ቀን›› ማግስት ማክሰኞ ጥቅምት 20/ 2005 ዓ/ም ሳምንታዊ መሰናዘሪያ ጋዜጣ ላይ ‹‹እውን ኢህአዴግ ሰንደቅ አላማውን ያከብረዋልን?›› የሚል ጽሁፍ ጽፌ ነበር፡፡ እኔ ከመስሪያ ቤት የተባረርኩበት የሰንደቅ አላማው ጉዳይ አሁን ወደ መሰናዘሪያ ዞረ፡፡ ከሰንደቅ አላማው ይልቅ ለአቶ መለስ ክብር የሚሰጠው ኢህአዴግ መሰናዘሪያ ዳግመኛ እንዳትታተም በማተሚያ ቤቶች ላይ ጫና አደረገ፡፡ እኔን ከመስሪያ ቤት ያባረረኝ ኢህአዴጋዊ የአቶ መለስ ክብር መሰናዘሪያን አሳገዳት፡፡ ይህም ከአንድም በሁለት ሶስት ህግ ስለ ሰንደቅ አላማው አስፍሮ፣ ወጭ አውጥቶና ቀን ቆርጦ ለሰንደቅ አላማው ቀን ‹‹እያከበረ›› የሚገኘው ኢህአዴግ በእውኑ ለሰንደቅ አላማው ክብር እንደማይሰጥ ያሳያል፡፡ ይህ እርምጃ ግን የተወሰደው በእኔ ብቻ አይደለም፡፡ የሰንደቅ አላማ ቀን መከበሩን ተከትሎ ኢህአዴግ በግዳጅ ‹‹በዓል አክብሩ›› ያላቸው በርካታ ወጣቶች ሰንደቅ አላማው ‹‹ጨርቅ›› መባሉን በመከራከሪያነት በማቅረባቸው መባረራቸውን ሰምቻለሁ፡፡ ኢህአዴግ ጥፋቱን አምኖ ለሰንደቅ አላማው ክብር እስካልሰጠ ድረስ በቀጣይነትም ጥያቄ ያነሱ ኢትዮጵያውያን ይባረራሉ፡፡ ተቋማትም ይዘጋሉ፡፡
ኢህአዴግ ያኔ አቶ መለስ ሰንደቁን ‹‹እራፊ›› ሲሉም ሆነ ሲዘቀዝቁት ይቅርታ አልጠየቀም፡፡ ለአቶ መለስ ሲል በአዋጅ የጸደቀውን የሰንደቅ አላማ ቀን እንደፈለገው ሲያራዝም ጥፋት መስሎ አልታየውም፡፡ ታዲያ በሰንደቅ አላማው ላይ ይህን ሁሉ ጥፋት የፈጸመው ኢህአዴግ ሰንደቅ አላማው ላይ ጥፋት ፈጽመዋል በሚል በሌሎች ላይ ክስ ለመመስረት ሞራል ከየት አገኘ? ካልሆነ ህገ መንግስቱና አዋጁ ከኢህአዴግ ውጭ ለሚገኙት ኢትዮጵያውያን ነው የሚሰራው እንደማለት ነው፡፡
እስካሁን በዓለም የራሱን ሰንደቅ አላማ የተሳደበ ጠቅላይ ሚኒስትር፣ ፕሬዝዳንት አሊያም ፓርቲ ተሰምቶ አይታወቅም፡፡ ይህ የኢህአዴግ ብቸኛ መገለጫ ነው፡፡ በተቃራኒው ሰንደቅ አላማውን ያከበረ የሚያስመስልባቸው ህጎችና አዋጆች ሰንደቅ አላማቸውን ከልብ ከሚወዱ ስርዓቶች ‹‹በመልካም ተሞክሮነት›› ቃል በቃል የተገለበጡ ናቸው፡፡ ለአብነት ያህል የብሪታኒያ ፓርቲዎች ለሰንደቃቸው ትልቅ ክብር ከሚሰጡት መካከል ይመደባሉ፡፡ ኢህአዴግ አጽድቆ የሚጥሰው ‹‹የሰንደቅ አላማ ቀን››ም ሆነ ‹‹አዋጅ›› ከብሪታኒያ ጋር ተመሳሳይነት አለው፡፡ ሆኖም ብሪታኒያውያን ለራሳቸው ሰንደቅ አላማ ይቅርና ለሌሎቹም ክብር ይሰጣሉ፡፡ ለምሳሌ ያህል ባለፈው የለንደን ኦሎምፒክ ከሰንደቅ አላማ ጋር በተያያዘ አንድ ስህተት ተፈጽሞ ነበር፡፡  በኦሎምፒኩ ወቅት የሰሜን ኮሪያ የሴቶች የእግር ኳስ ብሄራዊ ቡድን እየተዋወቀ እያለ ቴሊቪዥን ላይ ይታይ የነበረው ሰንደቅ አላማ የደቡብ ኮሪያ ነበር፡፡ ለዚህ ስህተትም በተለይ በሰሜን ኮሪያውያን ዘንድ የኦሎምፒኮ አዘጋጆች ብቻ ሳይሆኑ ብሪታኒያ ራሷም ተወቅሳለች፡፡ ብሪታኒያውያን ይህንን ወቀሳ የኦሎምፒኩን አዘጋጆች፣ የብሪታኒያ መሪዎች አሊያም ብሪታኒያን ‹‹ክብር አዋረደ›› ብለው መስል አልሰጡም፤ እርምጃ አልወሰዱም፡፡ ይልቁንስ የብሪታኒያው ጠቅላይ ሚኒስትር ለተፈጠረው ስህተት በዓለም አቀፍ ደረጃ ይቅርታ ጠይቀዋል፡፡ ስህተቱን የፈጸሙት የብሪታኒያ ጠቅላይ ሚኒስትር አልነበሩም፡፡ ሆኖም ለሌላ አገር ሰንደቅም ያላቸውን አክብሮትና የተፈጸመውን ጥፋት በይቅርታቸው አምነዋል፡፡ የብሪታኒያ ገዥዎች በራሳቸው ላይ ብቻ ሳይሆን በሌላ አገር ሰንደቅ አላማ የሚፈጸም ስህተት ላይ የመክሰስ፣ የመቃወምና የመተቸት የሞራል ልዕልና ይኖራቸዋል፡፡ ሙስሊሞቹ ሲያውለበልቡት ነበር ያለውን የተበጣጠሰ ሰንደቅ አላማንም በሰንደቅ አላማ የማያምንበት ኢህአዴግ እንዴት  ጥብቅና ለመቆም ይቻለዋል?
ኢህአዴግ የሚያደርገው ከዚህም በተቃራኒ ነው፡፡ ራሱ ህግ አውጥቶ፣ አዋጅ አጸድቆ፣ በዓል ‹‹እያከበርኩ ነው›› እያለ፣ እራሱ የቀየረውን ሰንደቅ አላማ አሁንም እያወረደው ነው፡፡ ከጣሊያን ቀጥሎ ደግሞ ለረዥም አመት የኢትዮጵያን ሰንደቅ አላማ እያዋረደ ይገኛል፡፡ በመሆኑም እስካሁን በተፈጸሙት ላይ ህዝብን ይቅርታ ሳይል ሌሎች ሰንደቅ አላማውን እንደማየከብሩት ለማሳጣት መሞከሩ አሁንም ከራሱ ጠባብ ቡድናዊ ጥቅም የዘለለ ነው ለማለት ያስቸግራል፡፡ ሰንደቅ አላማው ከኢትዮጵያውያን አልፎ በዓለም ህዝቦች ዘንድ ዝና እና ተቀባይነትን ያተረፈው ህገ መንግስትም ሆነ አዋጅ ሳይወጣለት ነው፡፡ ኢህአዴግ ደግሞ ስፍር ቁጥር የሌለው ህግ አውጥቶ እራሱ እየጣሰ ሌሎችን ለመክሰሻነት ብቻ እየተጠቀመበት ነው፡፡ መቼም ከአሁን በኋላ ሰንደቁን የሚያዋርድ የውጭ ሀይል ይበጣል ተብሎ አይገመትም፡፡ ኢህአዴግ እስካለ ድረስ ግን ሰንደቁ እንደተዋረደ የሚቀጥል ይመስላል፡፡ ከኢህአዴግ ውጭ ያሉት እንኳን ሰንደቁን ቢያዋርዱት ያዩት ከእሱው ነው፡፡ ‹‹መንግስት››ን ያህል ነገር የተቆጣጠረ ፓርቲ፣ የጠቅላይ ሚኒስትርነትን መንበር የተቆናጠጠ አካል ሰንደቁን ሳያከብር ማን ሊያከብረው ይችላል? ህጉን ለማጥቂያነት ብቻ የሚጠቀምበት ኢህአዴግ ሰላማዊ ሰልፈኞቹ ‹‹ለሰንደቁ ክብር የላቸውም›› የሚል ፕሮፖጋንዳውን አጠናክሮ ቀጥሏል፡፡ በእርግጥ ይህ የተጀመረው በሙስሊሞቹ ብቻ አይደለም፡፡ ሰማያዊ ፓርቲ ባዘጋጀው ሰልፍ ላይም ሰልፈኞቹ ‹‹ሰንደቅ አላማውን አዋርደዋል›› ተብለው ተከሰዋል፡፡ ሰንደቅ አላማ በኢትዮጵያውያን ዘንድ ምን ያህል ቦታ እንዳለው የሚያውቀው የኢህአዴግ ‹‹መንግስት›› ሰንደቁን ከማክበር ይልቅ ሌሎቹ እንደማያከብሩት በመምቻነት በስፋት እየተጠቀመበት መሆኑ ያሳየናል፡፡
ይህን ጽሁፍ ዳግመኛ ስጽፍም ሆነ ስለ ሰንደቁ ለሶስተኛ ጊዜ ሳነሳ ከሰንደቁ ይልቅ ለአቶ መለስ ክብር የሚሰጠው ኢህአዴግ የሚወስደው እርምጃ አላሳሰበኝም፡፡ በአባቶታችን ደም የተቀለመው ይህ ሰንደቅ አላማ ከስራ ከመባረርና ከመሳሰሉት ‹‹ጥቃቅን›› እንቅፋቶች በላይ በርካታ መስዋትነት ተከፍሎበታልና!

Saturday, August 24, 2013

ሃይማኖትና ፖለቲካ በኢትዮጵያ (ዶ/ር ብርሃኑ ነጋ)


August 21, 2013
ዶ/ር ብርሃኑ ነጋ
1. መግቢያ:
ካለፈው ሁለት አመት ግድም ጀምሮ “መንግሥት በዲናችን ጣልቃ አይግባብን” በሚል ሰፊ ማእቀፍ ውስጥ በሰላማዊ መንገድ በኢትዮጵያውያን ሙስሊሞች እየተደረገ ያለው ትግል፤Ginbot 7 movement chairman Dr. Berhanu Nega በኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን ውስጥ ደግሞ ሁለት አስርት አመታትን ያስቆጠረ ከቀኖናው ውጭ መንግሥት የቤተክርስቲያኑን መሪ አይምረጥብን በሚል በመሰረታዊ ሀሳቡ ከሙስሊሙ ጥያቄ ጋር ተመሳሳይ በሆነ ጉዳይ በተነሳ ውዝግብ ቤተክርስቲያኒቱ ለሁለት ተከፍላ ያለችበት ሁኔታና በዚህም ምክንያት በመንግሥት የተገፋው “ስደተኛው ሲኖዶስ” በራሱ ላይ የደረሰውን ሁከት በመቃወም የሚያደርጋቸው እንቅስቃሴዎች ተዳምረው ምናልባት ለመጀመሪያ ጊዜ ጤነኛ የሆነው የሀይማኖትና የፖለቲካ ግንኙነት ምንድን ነው? ወይንም ደግሞ የመንግሥትና የሀይማኖት ግንኙነት ምን መሆን አለበት? የሚለውን ጥያቄ ጉዳዩ በቀጥታ ከሚመለከታቸው የሀይማኖቱ ተከታዮች አልፎ ያጠቃላይ የፖለቲካ ማህበረሰቡ (የሀገሩ) ትልቅ የመወያያ አርዕስት እየሆነ ነው:: ይህ ጉዳይ ግን ጥቅል ከሆነ ያመለካከትና የንድፈ ሀሳብ ጥያቄ በተጨማሪ ጥልቅና አስቸኳይ የሆነ የተግባር ፖለቲካ ጥያቄም ነው ይዞ የመጣው::

Yehenene Yezergea Mengest Landem Lmechersham Geze Tageln Masweged Yeyandandachen Gedeta Naw !!!

አሳ ጐርጓሪ ዘንዶ ያወጣል (ክፍል ፭)


August 22, 2013
ናደዉ፦ከዋሽንግተን ዲሲ
የወያኔ ጉጅሌዎችን ስዉር አጀንዳ ፅሁፍ ከዚህ ሆድ አደር ተላላኪ ታሪክ በኋላ ወደ ሌሎቹ እዘምታለሁ፤በማህበር ተጠርንፈዉ እስከሚመጡልኝ ወይም እስከሚመጡብኝ ድረስ ማጋለጤ በሰፊዉ ይቀጥላል፧ለጠላቴ አልተኛም እንደ በትናቸዉ/ፍርሻው ስንሻዉ የታች አርማጭሆ ልጅ መሆኔ ቀረ?!
ምርጫዉ ስንሻዉ ወይም ብዙዎች የዲሲና አካባቢዉ ነዋሪዎች እንደሚጠሩት በትናቸዉ/ፍርሻው ስንሻዉ ባለፈዉ እሁድ ደግሞ አዲስ የጥላቻና የጋጠወጥ ስድብ ከረጢቱን ዘረገፈዉ፣ አዎ በዋሽንግተን ዲሲ አካባቢ በሚገኙት በሙስሊሙ ሕብረተሰብ መሪ በፈርስቲ ኢጂራ ፕሬዘዳንት በሼክ ነጂብ ላይ፧ በወያኔ ጉጅሌ በጀት በሚተዳደረዉ ወናፍ መንደርተኛ ራዲዮኑ እሳቸዉን ብቻ ሳይሆን ባለቤታቸዉንና የሙስሊሙን ሕብረተሰብ የድምፃችን ይሰማ እንቅስቃሴም ጭምር፥እንደወያኔ አስተዳዳሪዎቹ ሁሉ እሱም ሲሳደብ ዉሎ አደረ ፧ተወካያቸዉ መሆኑም አይደል?!መሽቶ ነጋ በቅዳሜ ማታና በእሁድ ቀን ፕሮግራሞቹ፤እኔም በዚህ ባንዳ ዙርያ በተከታታይ ለማወጣቸዉ ፅሁፎቼ ስል አለፍ አለፍ አድርጌ መቅረፀ ድምፄን ይዤ መከታተሌ አልቀረም፧ሚስቴና ልጆቼን ተደብቄ በሌሉበት መሆኑ ይታወቅልኝ !ምክንያት፥የዚህን ተሳዳቢ ሰዉዬ ቱማታ ላለመስማት ቤቱን ጥለንልህ እንዉጣ የሚለዉ ብስጭታቸዉ ስላሳሰበኝ ብቻ !!
ለእለቱ ለስድብ ኢላማነት የተመረጡትን እኝህን የሀይማኖት መሪ እንዲህ አለ፦ በአክብሮት ዘለፋዬን እርስዎም ባለቤትዎም የሀይማኖትዎም ተከታዮች በጥሞና ያዳምጡኝ ብሎ የራዲዮን ፕሮግራሙን ጀመረ፣የተለመደዉን የጥላቻ ስድብ ዉርጅብኝ በይሉኝታ ቢስና ፀያፍ ቃላቶቹ ለቀቀዉ አዎ እሱ ማንን ፈርቶ?!
ዛሬ ገና ለዚህ ተከታታይ ፅሁፌ ተገቢና ትክክለኛ ርእስ መስጠቴን አረጋገጥኩ። አሳ ጐርጓሪ ዘንዶ ያወጣል። ያልኩትን፧ በትምህርተ ጥቅስ አስቀመጥኩት፤ ለምን እንዲህ አልክ ብትሉኝ መልሴ እንደሚከተለዉ ይሆናል፧! እኚህ ሰዉ ስለዚህ መሰሪ የደርግ ካድሬ ብዙ ምስጢር እንደሚያዉቁ ስለማዉቅ ብቻ ሳይሆን ዛሬ የሚያዉቁት ነገር ምናልባትም ላለፉት አስርተ አመታት ለዋሽንግተን ነዋሪ ኢትዮጵያዉያን ያልተናገሩትን የደራሽ ግብረሃይል ምስጢር የሚያጋልጡበት ወቅት አሁን በመሆኑ ነዉ። ሳይቸግረዉ የነካካቸዉ ይመስለኛል፧ያዉም የሞራል ህልዉናን በሚፈታተን መልኩ፥ለዚህ ወስላታ የመልስ ምት አያስፈልገዉ ብለዉ ነዉ ሃጂ?! ነገሩ እንዲህ ነዉ በክፍል አንድና ሁለት ላይ በግልፅ እንዳሠፈርኩት የዛሬ አስር አመት አካባቢ አገራችን ኢትዮጵያ በከፍተኛ ረሀብና ድርቅ በተጠቃችበትና አላፊነት የጎደለዉ የህወሀት ዘረኛ አምባገነን አገዛዝም ሁኔታዉን ለመደበቅ በሚድበሰበስበት በዚያን ወቅት የዓለም አቀፍ የዜና ማሰራጫዎች ሁኔታዉን ገሀድ ማዉጣታቸዉ እርግጥ ነዉ። በወገኖቻችን ላይ ደርሶ የነበረዉ አስከፊ ሁኔታ ወያኔን ከመታገል ጎን ለጎን ለተጎዱት ወገኖች በአፋጣኝ መድረስ ጊዜዉ ግድ ይል ነበር። በዚህም መሰረት በዳያስፓራ የሚገኙት አገር ወዳድ ኢትዮጵያዉያን ትልቅ ድርሻ አበርክተዋል በዋሽንግተንና አካባቢዉም በተመሳሳይ መልኩ ከተጎጂ ወገኖቻቸዉ ጎን ለመቆም መንቀሳቀሳቸዉ አልቀረም። ይህንኑ የወገን ጥሪ ምላሽ ለመስጠት ሲባል በተቋቋመዉ የገንዘብ ማሰባሰቢያ ግብረሃይል ዉስጥ ከፍተኛ ተሳትፎ በማድረግ ከሁለት መቶ ሽህ ዶላር በላይ ተሰበሰበ የተሰበሰበዉንም ገንዘብ ደራሽ ግብረሃይል የሚል ስያሜ ለተሰጠዉ ኮሚቴ በአደራ በአደራ አስረከበና ዉጤቱን መጠባበቅ ጀመረ። በጊዜዉ ከኮሚቴዉ አባላት ዉስጥ በግምባር ቀደምትነት የሚጠቀሱት የኢትዮጵያዊነት ራዲዮኑ ጓድ ምርጫዉ ስንሻዉ፤የሀገር ፍቅር ራዲዮኑ ባንዳዉ ንጉሴ ወልደማርያም፤የፈርስቲ ኢጅራዉ ፕሬዘዳንት ሃጂ ነጂብና ሲስተር እማዋይሽ ነበሩ። ተወካዮቹ በአካል ተገኝተዉ ለተጎጂ ወገኖቻችን አስፈላጊዉን ቁሳቁስ ገዝተዉ አንዲሰጡ የሕዝብ አደራ ተቀበሉ ፧አደራዉን ግን በሉት።
እንዲህ ሆነላችሁ የተከበራችሁ ኢትዮጵያዉያን ወገኖቼ፧ የኮሚቴዉ ተወካዮች አዲስ አበባ ቦሌ አለምአቀፍ አዉሮፕላን ማረፊያ እንደደረሱ በወያኔ ካድሬዎችና ሰላዮች ታጅበዉ ወደተዘጋጀላቸዉ ሸራተን ሆቴል አመሩ፧ ከተለያዩ ባለስልጣኖችም የምስጋናና የእንኳን ደህና መጣችሁ ስልኮች አቃጨሉላቸዉ የኰሚቴዉ መሪ የነበረዉ ሆድ አደር ተላላኪዉ ንጉሤ ወልደማርያም ከመመሪያ ጋር በእለቱ በሆቴል ክፍሉ ዉስጥ የወያኔ አባልነት ፎርም መሙላቱን የከብት ሕክምና ባለሙያዋ ባለቤቱ ታወራለች። በተያዘላቸዉ ምርጥ ክፍል አርፈዉ ለጥቂት ቀናት በከተመዉ ዉስጥ ከተዝናኑ በኋላ ፧ከየአቅጣጫዉ ከአገር ዉስጥም ሆነ ከዉጭ አገር በተጎጂዎች ስም በሚጎርፍለት ገንዘብ የሰከረዉ ወያኔ መልእክተኞቹን በቴሌቪዥን መስታወት ለጥቂት ደቂቃዎች ከሌሎች ለጋሾች ጋር ቀርበዉ ሁለት መቶ ሽህ የኢትዮጵያ ብር በጊዜዉ የወያኔ የአደጋ መከላከል ኰሚሽን ኮሚሽነር ለነበሩት ለአቶ ስምኦን መቻሌ ያስረክቡና በሌላ የክህደት ፕሮግራም ለመገናኘት ተማምለዉ ይለያያሉ። ከመሐል አንድ እህታችን ብቻ በነገሩ ግራ በመጋባት ይህንን የህዝብ አደራ በልነትን ታወግዛለች ወደ አሜሪካ ስትመለስ ለማጋለጥም ለራሷ ቃል ትገባና ዋሽንግተን በገቡ ማግስት ጀምሮ በተለያዩ ራዲዮኖች እየቀረበች ወገኖቼ የረሀብተኛዉ የእርዳታ ገንዘብ ተበላ እያለች መጮህዋን ትቀጥላለች ፧ቀሪ የኰሚቴ አባላትን ጨምሮ በአማላጅ ሁኔታዉ ይፋ እንዲወጣ ታስጠይቃለች ነገር ግን የሚሰማት ጠፋ ። አንድ እለት ብቻ ጓድ በትናቸዉ ስንሻዉ ከሕብረተሰቡ ዛቻና ማስፈራርያ ሲበዛበት በራሱ ራዲዮ ላይ ወጥቶ ሃምሣ ሽህ ዶላር ብቻ መቅረቱንና ይህም ገንዘብ ወደፊት የሕዝብ ዉሳኔ ያገኛል ብሎ ለፈፈ፤ከዚያ ቀናት ሳምንታትን ሳምንታት ወራትን ወራት አመታትን አስቆጠሩ እነሆ ዛሬ አስርተ አመቱ ተቆጠረ ነገሩ የተረሳ ከሀዲ ቀማኞቹም ለይቶላቸዉ ወያኔ በፍርፋሪ ከጎኑ በግልፅና በስዉር አሰልፏቸዉ በሚመፀወቱት የራዲዮን የአየር ሰአት እንደገና ይሰድቡናል ያላግጡብናል፣ ገንዘቡንና ጊዜዉን የተበላዉ ነዋሪም አፈር ብላ ብሎ ተራግሞ ወደ ቤቱ ገባ ብዙዎች ግን በተለያዩ ቦታዎች የነዚህን ከሀዲዎች ፀያፍ ተግባር ዛሬም ያስታዉሳሉ። ይህ የህዝብ ገንዘብ ነዉ ያለንበት አገር ደግሞ የህግ የበላይነት ይከበራል የተበላዉ በረሀብ ለተጎዱ ወገኖች የተዋጣ ገንዘብ ነዉ የፈለገዉ ያህል ጊዜ ቢቆይም ጉዳዩን በሕግ ፊት ማቅረብ ይቻላልና የህግ ባለሞያ ኢትዮጵያዉያንን ነገሩን እንዲመረምሩት በዚህ አጋጣሚ አሳስባለሁ!
አሁንም በቅርቡ በዚያ በዘራፊዎቹ ንኡስ ኰሚቴ ዉስጥ የነበሩ አዛዉንትን አግኝቼ ሳነሳባቸዉ ነገሩ እንደዉስጥ እግር እሳት ያንገበግበኛል አሉ ወንጀለኞቹን እነ በትናቸዉ ስንሻዉን ዛሬም ምርር ብለዉ በፊቴ ተራገሙ በተጨማሪም እንዲህ አሉኝ በዚያን ወቅት ተጨንቄ ሃጂ ነጂብም ዘንድ ሄጄ እዉነቱን ለሕዝቡ ንገሩ ብዬ ብጠይቀዉ ዳግም አጠገቡ እንዳልደርስ አባረረኝ አሉና ሁኔታዉን ጊዜ እንዳመቻቸዉ የሚያዉቁትን ሁሉ በተገኘዉ ሚዲያ ገሃድ እንደሚያደርጉት ገለፁልኝና ተሰነባበትን።
በመጨረሻ ማሳሰብ የምወደዉ ሃጂ ነጅብ የሚያዉቁትን ይንገሩንና እርስዎም ከሕሊና ወቀሳ ይገላገሉ፣በብዙ ሀይማኖቶች ሲነገር የምንሰማዉ፦ ሌባና ሌባ ሲሰረቅ አይቶ እንዳላየ የሆነ ፧የሁለቱም ወንጀል አንድ ነዉ ይባል የለ?!እና እነዚህ ወሮበሎች ስለዘረፉት ገንዘብ የሚያውቁትን ይንገሩን እግረመንገድዎንም ከሃሜቱ ነፃ ይዉጡ እያልኩ ነዉ። ወቅቱም አሁን ነዉና!!!
የጓድ በትናቸዉ ስንሻዉ ጉድ መቸም ቢጎለጎል አያልቅም እኔም አንዴ ጀምሬዋለሁና የማዉቃቸዉንና የሚደርሱኝን መረጃዎች በሙሉ እሄድባቸዋለሁ አዲስ አበባ አፍንጮ በር አካባቢ ለምትኖረዉ የድሮ ጓደኛዪ ምሥራቅ ስንሻዉ ከባለቤትዋ ከታጋይ ተክሌ አጋበዝ ጋር ሆና የወንድምዋን ጉድ እንድታየዉና ይህንን ፅሁፍ እንድትፈትሸዉ ሰሞኑን ሳልደዉልላት አልቀርም።
ይህን ማስታወሻ ስፅፍ ዶክተር ታዬ ወልደሰማያትና አቶ ብርሃነ መዋ ትዝ አይሉኝ መሰላችሁ!?በነገራችን ላይ ሁለቱንም ወንድሞቼን እጅግ አድርጌ አከብራቸዋለሁ በኢትዮጵያ ፖለቲካ ዉስጥ ቀላል የማይባል አስተዋፅዖ ማበርከታቸዉ እውነት ነው። ዛሬ ግን ወደ ፓለቲካዉ መድረክ ዳግም ላይመለሱ ከአንደበታቸዉ ብዙዎቻችን ሰማን። የሚገርማችሁ ደግሞ ሁለቱም በአንድ ወቅት በቅንጅት መፍረስ ማግስት መሆኑ ነዉ፧ ለዚህ ትልቁና ዋናዉ ተከሳሽ ጓድ በትናቸዉ ስንሻዉ መሆኑ አይደንቅም። የቅንጅት አመራሮች በእስር ላይ በነበሩበት ግዜ እዚህ የነበሩት የቅንጅት የድጋፍ ኮሚቴ አባላት መከፋፈል ጀመሩ የኰሚቴው ሰብሳቢ የነበሩት ሻለቃ ዮሴፍ በእስር ላይ ከሚገኙት የቅንጅት ፕሬዘዳንት ከኢንጅነር ሃይሉ ሻወል የኰሚቴ አባላቶች ሹም ሽር በፊርማቸዉ አረጋግጠዉ ላኩ ተባለ አሰራሩ ማእከላዊነት ያልጠበቀ ነዉ ይሄ የንጉሣዊ ሹመት አይነት ነዉና አንቀበልም የሚል አካል ተፈጠረ የነብርሃነ መዋ ቡድን፧ ከስር ቤት ሾልኮ መጣ በተባለዉ የሹመት ዝርዝር ዉስጥ በዚያ የፓርቲ ስብስብ ዉስጥ ያልነበሩት የዶክተር ታየ ወልደሰማያት ስም የመሪነቱን ቦታ ይዞ ቀረበ ይህንን ሁኔታ በከፍተኛ ደረጃ እንዲያራግቡት ሃላፊነቱን በበላይነት አንዲመራዉ ደጎስ ካለ የገንዘብ ጉርሻ ጋር ጓድ ምርጫዉ ስንሻዉ ተረከበ ረዳት ሆድአደር አፍራሾችም ተመደቡለት ረዳቶቹ ደግሞ ከኛ ወዲያ ትግል ላሳር የሚሉ የትግል ዘመናቸዉን ሻማ በማብራት ብቻ የሚደክሙ የዲሲ ፋኖዎችና በታኞች ተሳካላቸዉ በአጭር ጊዜ የአገሪቱን ሕዝብ አንድ አድርጎ ወያኔን ያርበደበደዉን ብዙ ዜጎች በጠራራ ፀሐይ ዉድና ተተኪ የማይገኝለትን ዉድ ሕይወታቸዉን የገበሩለትን የፓለቲካ ንቅናቄ ጠልፈዉ ጣሉት አሽመደመዱት። አዎ ምርጫዉ ስንሻዉ፧እነ ሻለቃ ዮሴፍንና ታዋቂዉን ስመ ጥር የፖለቲካ ሳይንስ ምሁር ማኖ አስነካቸዉ ሸወዳቸዉ በግርግርም ከፍተኛ ገንዘብ ተበላ ቅንጅትም ለአንዴና ለመጨረሻ ግዜ ከጨዋታ ዉጪ ሆነ ተበተነ የበትናቸዉ ስንሻዉ አለቆች ከበሮአቸዉን ደለቁ ከሕዝባዊዉ ማእበል ተጠራርጎ ከመጥፋት ዳኑ፧ ያን ሁሉ ወንጀል ፈፅመዉ ዛሬም እነምርጫዉ አሉ!አሁንም ኢንጅነር ሐይሉን እነ ብርሃነ መዋንም ጨምሮ ሁሉንም ባልተገራዉ ግልብ ንግግሩ ሙልጭ አድርጎ እያወረዳቸዉ ነዉ።ዛሬ በዚህ ባንዳ ምክንያት ብዙ ጠንካራ ሰዎችን አጥተናል አሁንም ዘለፋዉን ቀጥሏል።
መቸም በበትናቸዉ ስንሻዉ ዘለፋና ዝርፊያ ቆሽቱ ያልተቃጠለ አንጀቱ ያላረረ የለምና የዚህ ካድሬ ተጠቂዎች ለዚህ ፅሁፍ አቅራቢ ብዙ መረጃዎች አደርሰዉታል፧ብዙዎቹ ይበሳጫሉ እንዲህ ያለ ኢትዮጵያዊ የለም ያስብላሉ ተግባራቶቹ ግን እዉነቶች ናቸዉ። እና አኔ እያልኩ ያለሁት ስም ለማጥፋት ለመጠፋፋት ሳይሆን አካሄድህ አስነዋሪ ነዉ ብሎ እሱነቱንና ወልጋዳ አካሄዱን ለራሱ እንደመስታወት አሳይቶ ወደወገኖቹ ለመመለስ ነዉ እንጂ ከተላላኪ ሆድ አደሮች ጋር ይሄን ያህል ግዜ ማባከን ባላስፈለገም ነበር ምናልባት ወደቀልቢያዉ ቢመለስ ብዬ እንጂ!!
ትናንት አንድ ወዳጄ አንድ አባት በዚህ አጉራ ዘለል ካድሬ የሆኑትን ልንገራችሁና የዛሬዉን ፅሁፊን ላብቃ በአንድ ወቅት ለከፈተዉ ቤተክርስትያን በደመወዝ እንዲያገለግሉት አንድ አባት ከምስጢራተ ቤተክርስትያንና ቅዱሳን መጽሐፍቶች ጋር ከአገር ቤት ያስመጣቸዋል በሚኖርበት አካባቢ ነዋሪዎች ቪላ ዉስጥ የምትገኝ አንድ ጠባብ ክፍል ይከራይላቸውና ይገባሉ ቄሱም በየወሩ ከሚሰጣቸዉ ደመወዝ ለቤቱ ኪራይ እየቀነሰ ቀሪዉን ሲሰጣቸዉ ይከርማል የሰዉየዉ ግልብ ባህርይ ባይመቻቸዉም ሌላ መጠጊያ ስለሌላቸዉ ረዘም ላለ ጊዜ እንደተቀመጡ እንባ እየተናነቃቸዉ ይናገራሉ አነጋገራቸዉ ሁኔታቸዉ በዚህ በመጦርያ እድሜያቸዉ ስደተኝነታቸዉና ሁኔታቸዉ እጅግ አሳዝኖኝ መንፈሴ እየተሸበረ ስላስቸገረኝ ንግግራቸዉን ቶሎ እንዲጨርሱ በመመኘት ከዚያ በኋላስ አልኳቸዉ ከዚያ በኋላማ ልጄ አሉ አንገታቸዉን አቀርቅረዉ መሬቱን በያዙት ረጅም ጃንጥላ ጫፍ እየቆረቆሩ ፦አንድ ቀን ትንሽ አመም አርጎኝ እቤት ዋልኩ ያለወትሮየ ቤት መዋሌን የተመለከቱት የቤቱ ባለቤቶች ሊጠይቁኝ መጡ እህል ዉሃም ሰጡኝና በደንብ ሳይሻለኝ እንዳልነሳ ሲመክሩኝ አይ እዚህ አገር ወጪዉ መች ያስተኛል አልኳቸዉ ሴትየዋም ሳቅ ብለዉ አይ አባ እርስዎ ደግሞ ምን ወጪ አለብዎት ለምግቡም ቢሆን አያስቡ አሉኝ እኔም ለሆዴ እንኳ ግድ የለኝም የቤት ኪራዩን ማን ይከፍልልኛል ስላቸዉ የምን የቤት ኪራይ ነዉ የሚያወሩት እኛ ሁኔታዎን አይተን ምርቃትዎ ይበቃናል ብለን ገንዘብ ተቀብለዉ አናዉቅም አሉኝ እኔም በየወሩ ከደመዜ ላይ እንደሚቆርጥብኝ ነገርኳቸዉና ከዚያን አለት ጀምሮ አይኑን አያሳየኝ ብዬ ለአምላኬ አልቅሼ ቀረሁ አሉኝ። አይገርምም ወገኖቼ?!
እነዚህን የመሳሰሉ አሳፋሪ ብዙ ተግባሮቹን ብዙ ትሰማላችሁ እዚህ አካባቢ ጎራ ብትሉ፤ከዚህ ነዉረኛ የወያኔ ተላላኪ የምንረዳው አንድ ነገር አለ ይኸዉም አምባገነኑና ጨካኑ የህወሀት ስርአት በዙርያው የሚኮለኩላቸዉ ፍርፋሪ ለቃቃሚዎች ምንአይነት ከርሳሞችና ምግባረ ብልሹዎች እንደሆኑ ነዉ።
ክፍል ፮ ይቀጥላል