Thursday, December 26, 2013

በአረና መጠናከር የሰጉት ህወሓቶች ‘ዕርቅ’ ፈፀሙ

በአረና መጠናከር የሰጉት ህወሓቶች ‘ዕርቅ’ ፈፀሙ

አብረሃ ደስታ ከመቀሌ
ህወሓቶች ለሁለት ተከፍሎው የደብረፅዮን (የአዲስ አበባ) ና የአባይ ወልዱ (የትግራይ) ቡድን ተሰይመው ሲነታረኩ መቆየታቸው ይታወቃል። ከወራት በፊት ጀምሮ ደግሞ ሁለቱም ቡድኖች ‘ለማስታረቅ’ ጥረት እየተደረገ መሆኑ ጠቅሼ ነበር።
ትንቅንቅ
ትንቅንቅ
አሁን አቶ ስብሃት ነጋ (ከቢተው በላይ ጋር በመሆን) ሁለቱም ባላንጣ ቡድኖች ‘ማስታረቅ’ ችለዋል። ዕርቁ የተፈፀመው በነ ደብረፅዮን ቡድን አሸናፊነት ነው። የነ አባይ ወልዱ ቡድን በመሸነፉ ምክንያት አቶ አባይ ወልዱ ከነ ስብሃት ነጋ ጋር እንዲስማማ ምክንያት ሁነዋል። የነ አባይ ቡድን የተዳከመበት ምክንያት ለሁለት በመከፈሉ ነው። አቶ አባይ ወልዱ ከአቶ ቴድሮስ ሐጎስ፣ ኢያሱ ተስፋይ፣ ተክለወይኒ አሰፋ፣ ኪሮስ ቢተው፣ በየነ መክሩ ወዘተ መግባባት ባለመቻሉ ከአዲስ አበባዎቹ ጋር ለመስማማት ተገደዋል።
tewedrosበስምምነቱ መሰረት ህወሓት በአዲስ አበባዎቹ ፕላን ይጓዛል። በ’መለስ ራእይ’ ስም ህዝብ መጀንጀን ይቀራል። በሙስና ሰበብ ባለስልጣናት ማሳሰርም ይቀራል። ከአሁኑ በኋል ከፍተኛ የህወሓት ባለስልጣናት በሙስና ሰበብ አይታሰሩም። በቀጣዩ የኢህአዴግ ጉባኤ የሀገሪቱ ጠቅላይ ሚኒስተር ከህወሓት እንዲሆን ጥረት ይደረጋል (ዶር ቴድሮስ አድሐኖም)።
ይህ የህወሓቶች የ’ዕርቅ ሂደት’ ባብዛኛው የብአዴን አመራር አባላትና በተወሰኑ የኦህዴድ መሪዎች ቅሬታ አስነስተዋል። ህወሓቶች ለመታረቅ የተገደዱበት ምክንያት በተቃዋሚዎች ስልጣን እንዳይነጠቁ በመስጋት ነው። ዓረና ፓርቲ ለህወሓቶች ትልቅ ስጋት በመፍጠሩ ነው። የፀጥታ ሃይሉ መፈራረስም ሌላ ህወሓቶች ያስደነገጠ ጉዳይ ነው። በዕርቁ ሂደት ከፍተኛ ሚና የተጫወተው አቶ ስብሃት ነጋ ነው።
የዕርቅ ሂደቱ በኢህአዴግ አባል ድርጅቶች ከፍተኛ አለመግባባት ሊፈጥር ይችላል። ኢህአዴግ በዉስጥ ለውስጥ የስልጣን ሹክቻ ምክንያት የሚዳከምበት አጋጣሚ መፈጠሩ አይቀርም። ዕርቁ ግዝያዊና ስትራተጂካዊ ብቻ ነው። የታረቁት መግባባት ስለ ፈጠሩ ሳይሆን የጋራ ጠላትን ለመከላከል ብቻ ነው።
Ze-Habesha Website may contain advice, opinions, and statements of various information and content providers. The Website neither represents nor endorses the accuracy of information or endorses the contents provided by external sources. All blog posts and comments are the opinion of the authors.

ሰበር ዜና ከሳውዲ አረቢያ ! ሮብ ምሽት በመንፈሃ ዙሪያ መጠነ ሰፊ ጥብቅ ፍተሻ ተጀመረ ! ነቢዩ ሲራክ

ሰበር ዜና ከሳውዲ አረቢያ ! ሮብ ምሽት በመንፈሃ ዙሪያ መጠነ ሰፊ ጥብቅ ፍተሻ ተጀመረ !

ነቢዩ ሲራክ
* በሪያድ የኢትዮጵያ ኢንባሲ የተጀመረውን ፍተሻ በማረጋገጥ ህጋዊ ሰነድ የሌላቸው ዜጎች በሰላማዊ መንገድ በአስቸኳይ ለጸጥታ አስከባሪዎች እጅ በመስጠት ወደ መጠለያ በመግባት ወደ ሃገር እንዲገቡ ማምሻውን ባወጣው ማስታወቂያ አሳስቧል ። ካለፉት ሳምንታት ወዲህ በሪያድ መንፉሃ በኢንባሲውና በሃገር ሽማግሌዎች የተቋቋሙ የመረጋጋት ኮሚቴ አባላት ወደ መንፉሃና ኢትዮጵያውያን በሚበዙባቸው ምንደሮች በመንቀሳቀስ ዜጎች ያለ ምንም ጉዳት እጃቸውን ሰጥተው ወደ ሃገር ለመግባት እንዲዘጋጁ የመከረ ቢሆንም ጥረቱ አልተሳካም ነበር ።  የሪያድ ኢናባሲ የሽማግሌዎች ኮሚቴ አባላት ባደረጉት ቅስቀሳ ወደ ሃገር ለመግባት ባልተጨበጠ ተስፋ የተዘናጉ ህጋዊ መኖሪያ ፈቃድ ያልያዙ ወደ ሃገር በመግባቱ ላይ እንዳያቅማሙ መምከራቸው ይጠቀሳል !
* አሁን በተጀመረው የመንፉሃ ፍተሻ ማዋከብ የለበትም ። ህጋዊ መኖርያ ፍቃድ የሌለውን ብቻ እንደሚይዙና ከአሰሪው (ከከፊሉ) ጋር ይሰራል አይሰራም የሚባል ማጣራትም ሲካሔድ አልተስተዋለም ተብሏል ።
* ከአሰሪው ጋር የማይሰራ እንደ ህገ ወጥ እንደሚቆጠር የሳውዲ ህግ በግልጽ ያሳወቀ ሲሆን የጅዳና የሪያድ ኢንባሲ ይህ ህግ እንደሚጸና ተደጋጋሚ ማስታወቂያ በማውጣት “በሰላም ወደ ሃገራችሁ ግቡ!” በማለት ሲመክሩና ሲወተውቱ ሰንብተዋል።
* በቀጣዩ መጠነ ሰፊ የማጣራት ዘመቻም ከአሰሪው (ከከፊሉ) ጋር የማይሰራ እንደ ህጋዊ ስለሚቆጠር የሳውዲ መንግስት በፈቃደኝነት እጃቸውን የሚሰጡት ወገኖች ወደ ሃገር መስደድ እንደተጠናቀቀ አንወጣም ባሉት ላይ ፍተሻ በማድረግ በእስራትና በገንዘብ እንደሚቀጣ በኢንባሲና በቆንስል መስሪያ ቤቶች በኩል ባስተላለፈው ማስጠንቀቂያ አስታውቋል ።
*  ቁጥራቸው በሽዎች የሚገመቱ ዜጎች እስካሁንም ድረስ ወደ ሃገር ግቡ የሚለውን ጥሪ ባለመቀበል የተዘናጉበት ሁኔታ ይስተዋላል ። ይሁን እንጅ ካለፉት ሁለት ቀናት ወዲህ መንቀሳቀስ  ያልጀመረው የጅዳ አካባቢ በርካታ ነዋሪዎች ወደ ሃገር ቤት ለመግባት ወደ ተዘጋጀው መጠለያ በመግባት ላይ ናቸው ። ከአሰሪያቸው ጋር ስለማይሰሩ ህገ ወጥ የተባሉት ግን አሁንም እንቅስቃሴ አለማሳየታቸው ይመለከታል ።
* የጅዳ ቆንስልና የወገን ለወገን ደራሽ ኮሚቴውም አውቶቡስን በአፋጣኝ እንዲቀርብ በማድረጉ ረገድ ከቆንሰሉ ሃላፊዎች ጋር በመተባበር ለነዋሪው ድጋፍ በማድረግ ላይ ናቸው ። ህጋዊ ሰነድ የሌላችሁ አስፈላጊውን ውሳኔ መውሰድና በእድሉ መጠቀም ይጠበቅችኋል። እድሉን መጠቀም መቻል ብልህነት ነው !
554190_613712818703643_1441333089_n
ጀሮ ያለው ይስማ
ነቢዩ ሲራክ

ከወያኔ ክፋትና እብሪት እንጂ ፍትህ አይጠበቅም


                   ወያኔ ባለፉት ሃያ ሁለት አመታት የአገራችንን የፍትህ ተቋሞች አንዴ አንደ ቂም መበቀያ ሌላ ግዜ ደግሞ እንደ ማጥቂያ መሳሪያ እየተጠቀመባቸዉ የፖለቲካ ተቀናቃኞቹንና ጥርስ የነከሰባቸዉን የህብረተሰብ አባላት እያሰረ፤ እያሳደደና እየገደለ ከርሞ ዛሬ ላይ ደርሷል። በተለይ ከግንቦት 1997ቱ ምርጫ በኋላ ወያኔ ብዕርና ወረቀት ይዘዉ በሃሳብና በአመክኖ የታገሉትን ሰላማዊ ዜጎች “ሽብርተኞች”፤ ድምጻችን ይሰማ ብለዉ የመብትና የነጻነት ጥያቄ አንግበዉ በሰላማዊ መንገድ የታገሉትን ኢትዮጵያዉያን የእስልምና እምነት ተከታዮች ደግሞ “አክራሪዎች” እያለ ፍርድ ቤት በማቅረብ በፍትህ ተቋሞች በኩል የፖለቲካ ዉሳኔ በማሳለፍ ሠላማዊ ዜጎችን ለረጂም ግዜ እስርና እንግልት ዳርጓል።
ወያኔ ለኢትዮጵያና ለዜጎቿ ደንታ የሌለዉ እና ከስህተቱ የማይማር የግብዞችና የዘረኞች ስብስብ ስለሆነ አሁንም የአገሪቱን የፍትህ ተቋሞች እንደ ማጥቂያ መሳሪያ እየተጠቀመ የኢትዮጵያን ህዝብ በፍርሃት ጨለማ ዉስጥ ሸብቦ እየገዛ ለመኖር የቆረጠ ይመስላል። ባለፈዉ ሳምንት አጋማሽ ላይ የወያኔ አገዛዝ ከአንድ አመት ተኩል በላይ እስር ቤት ዉስጥ አጉሮ ያቆያቸዉን የድምጻችን ይሰማ መሪዎች ከፊሎቹን በነፃ ተለቅቀዋል የሚል ከፊሎቹን ደግሞ ተከላከሉ የሚል ትርጉም የለሽ ብይን ሰጥቷል። በህወሀት ታጋዮች የተሞላዉ ፍርደ ገምድሉ የወያኔ ፍርድ ቤት እንኳን ተከሳሾቹ በተከሰሱበት ሽብር የመፈጸም ወንጀል ምንም አይነት ማስረጃ አልተገኘባቸዉም ሲል አገዛዙ ግን የፖለቲካ ክንዱን በመጠቀም ማስረጃ ያልተገኘባቸዉን ሠላማዊ ዜጎች የተከሰሱበትን መሰረተ ቢስ ክስ ተከላከሉ የሚል የፖለቲካ ዉሳኔ ሰጥቷል።
የወያኔ አገዛዝ የሙስሊሙን ህብረተሰብ የመፍትሄ አፈላላጊ ቡድን መሪዎች ፍርድ ቤት ያቀረባቸዉ ለምዕራባዉያን ለጋሾቹና ለአለም አቀፍ አበዳሪ ድርጅቶች ኢትዮጵያ ዉስጥ ፍትህ ያለ ለማስመሰል ነዉ እንጂ ወያኔ የድምጻችን ይሰማ መሪዎችን የፈረደባቸዉ ያሰራቸዉ ቀን ነዉ። የወያኔ የፍትህ ታሪክ በግልጽ እንደሚያሳየን ወያኔ ግለሰቦችን የሚያስረዉ ለክስ የሚያበቃ ማስረጃ አግኝቶባቸዉ አይደለም፤ ይልቁንም ወያኔ ማስረጃዎችን እየፈበረከ ለፍረድ ቤቶች የሚያቀርበዉ ግለሰቦችን ካሰረና ሰብዓዊ መብታቸዉን ከገፈፈ በኋላ ነዉ። ለምሳሌ የድምጻችን ይሰማ መሪዎችን አስሮ ብዙም ሳይቆይ የእነዚህን ሰላማዊ ዜጎች ተክለ ሰዉነት ጥላሸት የቀባና ግለሰቦቹን ያለ ማስረጃ ወንጀለኛ አድርጎ የፈረጀዉን “ጂሐዳዊ ሀረካት” የሚል የፈጠራ ድራማ ሰርቶ ለህዝብ አቅርቧል።
የፌዴራሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት ሽብር በመፈጸም ወንጀል ተጠርጥረዉ የቀረቡለትን ግለሰቦች በተከሰሱበት ወንጀል ማስረጃ አላገኘሁባቸዉም ካለ በኋላ ሁሉንም በነጻ አለማሰናበቱ የሚያሳየን የወያኔ ፍርድ ቤቶች ከፖለቲካ ተፅዕኖ ነጻ አለመሆናቸዉን ብቻ ሳይሆን፤ ኢትዮጵያ ዉስጥ ፍርድ ቤቶች የገዢዉ ፓርቲ የማጥቂያ መሳሪያዎች መሆናቸዉን ጭምር ነዉ። የወያኔን አገዛዝ ከሌሎች አምባገነኖች ለይቶ አደገኛ የሚያደርገዉና በምዕራባዉያን መንግስታትና በቀላጤዎቻቸዉ እንዲወደስ ያደረገዉም ይሄዉ አገዛዙ የሚቃወሙትን ኃይሎች የሚያጠፋቸዉ እንደሌሎቹ አምባገነኖች በግልጽ ሳይሆን በህግ ሽፋን ዉስጥ በስዉር መሆኑ ነዉ።
የወያኔዉ ፍርድ ቤት በተመሳሳይ ወንጀል ተከስሰዉ የቀረቡለትን ነገር ግን ምንም መረጃ ያላገኘባቸዉን የድምጻችን ይሰማ መሪዎች ገሚሶቹን በነፃ ለቅቆ የተቀሩትን ጥፋተኛ አለመሆናችሁን አረጋግጡ ብሎ መወሰኑ የወያኔን ሁለት እኩይ አላማዎች ያሳየናል። የመጀመሪያዉ የወያኔ አላማ በአላማቸዉ ጸንተዉ የቆሙትን የድምጻችን ይሰማ መሪዎች መከፋፈል ሲሆን፤ ሁለተኛ አላማዉ ደግሞ የኢትዮጵያ ፍርድ ቤቶች የቀረቡላቸዉን የክስ መዝገቦች በሚገባ አጣርተዉ ዉሳኔ የሚሰጡ መሆናቸዉን ለአለም አቀፉ ህብረተሰብ ለማሳየት ነዉ።
የኢትዮጵያ ህዝብ ግን እንደዚህ አይነቶቹን የወያኔ እኩይ ተግባሮች ካወቀ ዉሎ አድሯል፤ ስለሆነም ከወያኔ ፍትህ ጠብቆ አያዉቅም፤ ወያኔ የክፋትና የበቀል ምንጭ ነዉና ለደፊትም አይጠብቅም። የድምጻችን ይሰማ መሪዎችም ሆኑ ከእነሱ በፊት በግፍ ታስረዉ መከራቸዉን የሚያዩት የፖለቲካ ፓርቲ መሪዎች፤ ጋዜጠኞችና የሲቪክ ማህበራት መሪዎች የታሰሩት ለቆሙለት የፍትህ፤ የነጻነትና የእኩልነት አላማ እንደ አለት ጸንተዉ በመቆማቸዉ ነዉ። እነዚህ ጀግኖች የታሰሩለት አላማ የሁላችንም አላማ ነዉና ፍትህ፤ እኩልነትና ነጻነት የጠማን ኢትዮጵያዉያን ክንዳችንን አስተባብረን የችግሮቻችን ሁሉ ምንጭ በሆነዉ በወያኔ ስርዐት ላይ ክንዳችንን በጋራ እናንሳ!


    ድል ለኢትዮጵያ ህዝብ!!!

    Tuesday, December 17, 2013

    ''ፖለቲካ ሀጢአት ነው ወይ? '' የኢትዮጵያ ኦርቶዶክሳዊት ተዋህዶ ቤተክርስቲያን ሊቅ አጭር እና ግልፅ ምላሽ


    በሳምንቱ መጨረሻ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን ማኅበረ ቅዱሳን ወደ ደብረዘይት ደብረ መድሃኒት ኢየሱስ ክርስቶስ ቤተክርስያን  ባዘጋጀው የመንፈሳዊ ጉዞ ላይ በብዙ ሺህ የሚቆጠሩ ምዕመናን ተሳትፈዋል።መርሃግብሩ ላይ ከምዕመናን እና በቀጥታ በማኅበራዊ ድህረገፆች ለአባቶች የጥያቄ እና መልስ መርሃግብር ተዘጋጅቶ ነበር። ለተነሱ ጥያቄዎች ሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያን ምላሽ መስጠታቸው ከማኅበሩ የፌስ ቡክ ገፅ ላይ የተገኘው መረጃ ይገልፃል።ምእመናን ከእንደዚህ አይነት መርሃግብሮች እና ከሊቃውንቱ ቀጥተኛ እና  ትክክለኛ መረጃ ማግኘታቸው  ትልቅ ዋጋ ሊሰጠው የሚገባ ጉዳይ ነው።

    ከገፁ ላይ የተገኘውን ከእዚህ በታች እንዲህ ይነበባል-

    ''ቀጥሎ የሚኖረን መርሐ ግብር የጥያቄና መልስ መርሐ ግብር ሲሆን ሊቃውንቱ መልአከ ታቦር ተሸመ ዘሪሁን በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን የሊቃውንት ጉባኤ አባል፤ መጋቤ ሐዲስ ደጉ ዓለም ካሣ የቅድስት ሥላሴ መንፈሳዊ ኮሌጅ የሐዲሳት ትርጓሜ መምህር፤ መጋቤ ሐዲስ እሸቱ አለማየሁ በቅዱስ ጳውሎስ መንፈሳዊ ኮሌጅ የብሉይና የሐዲስ ትርጓሜ መምህር፤ ሲሆኑ ከምዕመናን ለሚቀርቡ ጥያቄዎች ደግሞ በዲ/ን ያረጋል አበጋዝ አቅራቢነት ያስተናግዳሉ፡፡ በዚህ አጋጣሚ ይመለስልን የምትሉት ጥያቄ ካላችሁ በውስጥ መስመራችንም ሆነ በ ኢ-ሜላችን ብትሉክልን እናስተናግደዋለን፡፡
    ……………………

    ጥያቄ 2 . ቅዱስ ጳውሎስ ሀገራችን በሰማይ ነው ስላለ እኛ ክርስቲያኖች በምድራዊት ሀገራችን ላይ እንዴት እንስራ?


    እግዚአብሔር ሰማይ ዙፋኔ ምድርም የእግሬ መረገ ናት እንዳለ አሁን ዛሬ ተቀምጠን የምንዘምርበት፣ የምንማርበት፣ የምናመሰግንበት፣ ይሄ ምድርም የእግዚአብሔር ፍጥረት ስለሆነ ሰው ለሀገሩም ሊሰራ ሊሞት ይገባዋል፡፡ ለዚህም ማሳያ የሚሆነው በአድዋ ድል የኢትዮጵያ ቤተክርስቲያንን ሱታፌ ማስታወስ በቂ ነው፡፡ መልአከ ታቦር ተሸመ ዘሪሁን የሊቃውንት ጉባኤ አባል
    ……………………..

    ጥያቄ 4 ፡ ፖለቲካ ሀጢአት ነው ወይ?

    ሰው በዚህ አለም ሲኖር ከሀጢአት በቀር በአለም ያለው ሁሉ ይመለከተዋል፡፡ በመጽሐፍ ቅዱስ እነ ዳዊት፣ እነሰሎሞን ፖለቲከኞች ነበሩ ስለዚህ ሀጢአት አይደለም ሀጢአት የሚሆነው አያያዙን ማወቅ ሲያቅት ነው፡፡ ወተት መጠጣት ሀጢአት አይደለም በረቡዕ ከተጠጣ ግን ሀጢአት ይሆናል፣ ቢላዎ ባለሞያ ሴት ካገኘችው ያገለግላል ባለጌ ካገኘው ሰው ይጎዳበታል ፖለቲካም አያያዙን ካወቅንበት ሀጢአት አይደለም፡፡ መጋቢ ሐዲስ እሸቱ ዓለምዓየሁ በቅዱስ ጳውሎስ መንፈሳዊ ኮሌጅ የብሉይና የሐዲስ ትርጓሜ መምህር።''
    በጉባኤው ላይ ከታደሙት ምዕመናን በከፊል 

    ይሄ ተንኮል ግን የህወሓት ዕድሜ ያራዝማል የሚል ግምት የለኝም።


    Posted: December 17, 2013 in Uncategorized
    0
    Abraha Desta
    ባለፈው ቅዳሜ ዓረና መድረክ በጠራው ህዝባዊ ስብሰባ ለመሳተፍ ወደ ማይጨው ከተማ ተጉዤ ነበር። ከመቀሌ -ማይጨው በመኪና የሦስት ሰዓት ጉዞ ነው። ከሰባት ዓመት በፊት የማውቃት ማይጨው ምንም አልተቀየረችም። ብዙ የህወሓት ባለስልጣናት እዛው ማይጨው ነበሩ። ስብሰባዎችና ስልጠናዎች ነበሯቸው።
    ቅዳሜ ከማይጨው ወጣቶች ጋር ተገናኝቼ ነበር። ወጣቶቹ ለውጥ ይፈልጋሉ። ግን ይፈራሉ። የሰለማዊ ትግል ዉጤታማነት ይጠራጠራሉ። ህወሓት በምርጫ ስልጣን ሊያስረክብ ይችላል ብለው አያምኑም። በሰለማዊ መንገድ ከሚቃወሙ በትጥቅ ትግል ቢሳተፉ ይመርጣሉ። ምክንያቱም በትጥቅ ትግል ህወሓት ከስልጣን የሚባረርበት ዕድል ሊኖር ይችላል ብለው ያስባሉ።
    በማይጨው የሚገኙ የመንግስት ሰራተኞችም (በተለይ መምህራንና የግብርና ሰራተኞች) በስርዓቱ ቅሬታ አላቸው። የራያ አከባቢ ተወላጆች የሆኑ የህወሓት ካድሬዎችም በስርዓቱ ደስተኞች አይደሉም። ሁሉም ለውጥ ይፈልጋሉ። ግን ዓረና ህወሓትን ታግሎ ሊያሽንፈው ይችላል የሚል እምነት የላቸውም። በራያ ቦታ የሚገኙ የህወሓት አባላት (የራያ ተወላጆች) ህወሓትን ማሸነፍ የሚችል ተቃዋሚ ፓርቲ ካገኙ ህወሓትን እንደሚቃወሙ ይገልፃሉ።
    የህወሓት መሪዎችም ይህንን ያውቃሉ። እንደዉጤቱም ህወሓት ከሌላ አከባቢ ታማኝ ካድሬዎች እየላከ የራሱ አባላት ይሰልላል፣ ይቀጣል፣ ያባርራል። በዚህ መንገድ የራያ ህዝብ በራሱ ሰዎች እንዲበደል ይደረጋል። የራያ ተወላጆች የሆኑ የመንግስት ሰራተኞች ለእንጀራቸው ሲሉ ህዝብ ይበድላሉ። ህዝብ ካልበደሉ ይቀጣሉ፣ ይባረራሉ፣ ሌላ የሚተዳደሩብት የስራ መስክ የላቸውም።
    የራያ ቦታ በህወሓት ከተረሱ አከባቢዎች አንዱ ነው። የራያ ህዝብ የክረምት ምግብ የነበረ ‘በለስ’ ለምርምር ተብሎ በገባ የሀር ትል ምክንያት ከጥቅም ዉጭ ሁነዋል። መንግስት የበለስ ጉዳቱ ለማካካስ የወሰደው እርምጃ የለም። በብዙ የራያ ቦታዎች የዉኃ ችግር አለ። የዉኃ ችግሩ ለመቅረፍ ብዙ ጉድጓዶች የተቆፈሩ ቢሆንም የዉኃ ቦይ ማስገባት ባለመቻሉ እስካሁን የዉኃ አገልግሎት የማያገኙ የራያ ቦታዎች አሉ።
    ከዓመታት በፊት ለመስኖ እርሻ እንዲዉል በጥናት መሰረት የተመረጠ ‘የጎልጎል ራያ’ ሜዳም እስካሁን አልተተገበረም። የህወሓት መሪዎች ጎልጎል ራያን በመስኖ የማልማት ዕቅድ ሰርዘውታል። ፕሮጀክቱ ለመሰረዝ የሰጡት ምክንያት በራያ የሚገኝ ዉኃ ‘ጨዋማ’ ስለሆነ ለመስኖ ጥቅም አይውልም የሚል ነበር። የሚገርመው ነገር ደግሞ አሁን ጎልጎል ራያ በኢንቨስትመንት ስም ለባለ ሃብቶች እየተሸጠ ነው የሚገኘው። ስለዚህ የህወሓት ሰዎች የጎልጎል ራያን በመስኖ የማልማት ፕሮጀክት የሰረዙበት ምክንያት ሰፊ ለም መሬቱ ለባለሃብቶች ለመሸጥ ስለፈለጉ ሊሆን ይችላል።
    የራያ ህዝብ ጀግናው ጥላሁን ይግዛውን ለመዘከር ሐውልት ለመገንባት ተብሎ ከራያ ተወላጆች ወደ 700,000 ብር የሚጠጋ ገንዘብ ከሰባት ዓመት በፊት የተሰበሰበ ሲሆን እስካሁን ድረስ ምንም ነገር አልተሰራም። የራያ ህዝብ ለጥላሁን ይግዛው ሐውልት ለመስራት የተሰበሰበ ገንዘብ የት እንዳለ ማወቅ ይፈልጋል፣ ይጠይቃል። አስተዳዳሪዎቹ የሰጡት መልስ ገንዘቡ ለኮብልስቶን አውለነዋል የሚል ነበር። ህዝቡም ኮብልስቶን የራሱ በጀት እንዳለው ሲከራከር ደግሞ አስተዳዳሪዎቹ ገንዘቡ የት እንዳለ እንደማያውቁ ይናገራሉ።
    በማይጨው አከባቢ በሚገኙ ተቋማትም የሙስና አሰራሮች መኖራቸው ኗሪዎች ይናገራሉ። በዚሁ ምክንያት የችፑድ ፋብሪካ፣ ማይጨው ግብርና ኮሌጅና ማይጨው ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ በተመሳሳይ ሁኔታና ወቅት የዳታ ኮምፒተሮች እንዲጠፉ ተደርገዋል። የዳታ ኮምፒተሮች እንዲጠፉ ሲደረግ ተቋማቱ ኦዲት እንዳይደረጉ ይረዳል። ኦዲት ካልተደረጉ ሙስና መሰራቱና አለመሰራቱ ለማወቅ ይከብዳል። የሙስና ጉዳይ ይፈተሽ።
    ቅዳሜ ማይጨው በነበርኩበት ሰዓት በከተማው የኢንተርኔት አገልግሎት አልነበረም። ለዚህም ነበር ስለ ማይጨው ሁኔታ በወቅቱ መፃፍ ያልቻልኩ (ኢንተርኔት መጠቀም የሚቻለው በሞባይል ብቻ ነበር)። በወቅቱ የዓረና የማይጨው ከተማ አባላት የማይጨው ህዝብ ዓረና ፓርቲ በጠራው የእሁድ ህዝባዊ ስብሰባ እንዲሳተፍ ይቀሰቅሱ ነበር። ህዝቡም ለዓረና ጥሩ አመለካከት ነበረው። የዓረና አባላት ‘ዓረና’ የሚል ፅሑፍ ያለው ነጭ ቲ-ሸርት ለብሰው ነበር የሚቀሰቅሱ።
    የህወሓት ሰዎችም ህዝብ በዓረና ስብሰባ እንዳይሳተፍ ለማድረግ የራሳቸው ቅስቀሳ ጀመሩ። ህወሓቶች ትልቅ ስፒከር ተጠቅመው በዕለተ እሁድ (በዓረና ስብሰባ) በማይጨው ከተማ የእግር ኳስ ውድድር ስላለ መላው ወጣት ተጫዋቾችን እንዲደግፍና እንዲያበራታታ ያውጁ ነበር።
    የራያ ተወላጆች ያልሆኑ ካድሬዎች ለራያዎቹ በእሁድ ቀን በሚደረገው የዓረና ስብሰባ ሰው እንዳይሳተፍ እንዲመክሩና እንዲያስፈራሩ ተነገራቸው (ይህ መረጃ የተገኘው ከካድሬዎቹ ከራሳቸው ነው)። በስብሰባው የተሳተፈም እንዲመዘግቡ ትእዛዝ ተሰጣቸው። በተጨማሪም ሰው ለመያዝ ሲባል የተለያዩ ያልታሰቡ የህዝብ ስብሰባዎች ተጠሩ። አብዛኛው የማይጨው ወጣት በራሳቸው ስብሰባ እንዲገኝ አዘዙት። የችኮማዮና የመኾኒ ‘ስራ አጥ’ ወጣቶች ‘ስራ እንዲሰጣቸው’ ለእሁድ ስብሰባ ተጠሩ። እሁድ በስብሰባው የተገኘ ስራ እንደሚሰጠው፣ ያልተገኘ ግን ስራ እንደማያገኝ ተነገረው።
    የማይጨው ህዝብም ለህወሓት ታሪክ ለመጀመርያ ግዜ የሙዚቃ ባንድ እንደሚመጣለት ሲነገረው ነበር። ህወሓት በማይጨው ከተማ የሙዚቃ ኮንሰርት ሲያዘጋጅ (ወይ አዘጋጃለሁ ሲል) ለመጀመርያ ግዜ ነው። ይህም ዓረና ህዝባዊ ስብሰባ በጠራበት ቀን ነው። እሁድ ቀን በስብሰባው ተሳታፊ ስለነበርን ህወሓቶች የራሳቸው ስብሰባ ስለማካሄዳቸው ሙሉ መረጃ አልነበረኝም። የሙዚቃ ኮንሰርቱ ስለ መሳካቱም እርግጠኛ አይደለሁም። የሙዚቃ ኮንሰርቱ ያልታቀደና ያልታሰበበት ስለነበረ ያልተሳካ ሙከራ ሊሆን ይችላል (ከተጋበዙት ሙዚቀኞች ቅሬታ ያሰሙ ነበሩ፤ በቂ ግዜ ስላልተሰጣቸው)።
    እሁድ ጠዋት ሰው ዓረና ወደ ጠራው ስብሰባ መግባት ከመጀመሩ በፊት የተወሰኑ የፀጥታና የፕሮፓጋንዳ ሐላፊዎች አደራሹ አከባቢ ተሰብስበው ነበር። ወደነሱ አከባቢ ስንሄድ ተበትነው ጠፉ። አብዛኞቹ የማይጨው ካድሬዎችና ፖሊሶች ግን ተባብረውናል። ተሳታፊ እንዲሰልሉና እንዲያስፈራሩ የተላኩ ካድሬዎች ከጎናችን ነበሩ። ‘እንደምንም ብላቹ ህወሓትን ማባረር የምትችሉ ከሆነ ከጎናቹ ነን’ ይሉን ነበር። ላደረጉልን ትብብር እናመሰግናለን። ህወሓትን ከስልጣን ማባረር የምንችል ግን ሁላችን ስንተባበር ነው።
    ህዝብ ወደ አደራሹ ገባ። ስብሰባውም ተጀመረ። እኛ ስለ ህወሓት መጥፎነትና የለውጥ አስፈላጊነት አወራን። ህዝቡም አስተያየት ሰጠ። ከህዝቡ የተረዳነው ነገር ቢኖር የራያ ህዝብ የህወሓትን መጥፎነት ከኛ በላይ ያውቃል። የህዝቡ ጥያቄ ህወሓትን እንዴት ከስልጣን ማውረድ ይቻላል? ዓረናስ አንዴ እየመጣ፣ ብዙ ግዜ እየጠፋ ህወሓትን ማሸነፍ ይችላል ወይ? ዓረናን ብንደግፍና ህወሓትን ከስልጣን ማባረር ባንችል ዋስትናችን ምንድነው? ህወሓት ሽፍታ ነው፤ ሊያጠፋን ይችላል ወዘተ የሚሉ ሐሳቦች ተነስተዋል።
    ህዝቡ በሰጠው አስተያየትና ትንተና ተገርምያለሁ። ህዝቡ ለውጥ ይፈልጋል። በህወሓት መሪነት እምነት የለውም። ህዝቡ ያጣው ነገር ህወሓትን ሊያባርር የሚችል ዓቅም ያለው የተቃዋሚ ፓርቲን ነው። ህዝቡ የሚመራው ፓርቲ ካገኘ ለመታገል ዝግጁ ነው። ዓረና ቆራጥነት ካለው ህዝቡ ከዓረና ጎን ተሰልፎ እንደሚታገል ቃል ገብተዋል።
    የማይጨው ስብሰባ ለየት የሚያደርገው ተሰብሳቢው በሙሉ የህወሓት ተቃዋሚ መሆኑ ነው። የህወሓት ካድሬዎች አልነበሩም። ሁላችን በአንድነት ለመታገል ቃል ስንገባ በአደራሹ የነበረ ሁሉ ቃሉ ሰጠ። አብረን ለመታገል ቃል ገባን። (ኩልና ብሓባር ንምቅላስ ንዓሪ ኢልና ዓረና)። ሦስት ሰዓት ተኩል የጀመረ ስብሰባችን ዘጠኝ ሰዓት ተኩል ተጠናቀቀ።
    እኔ የተረዳሁት ነገር አለ። የህወሓት ስጋት ዓረና አይደለም። የህወሓት ስጋት የህዝብ ማወቅ ነው። ህወሓት የትግራይ ህዝብ የፖለቲካ እውቀት እንዲኖረው አይፈልግም። ምክንያቱም የትግራይ ህዝብ የፖለቲካ ንቃተ ህሊናው ከፍ ካደረገ ለህወሓት ካድሬዎች አሜን ብሎ አይገዛም። ካልተገዛ ደግሞ የህወሓቶች ህልውና ያበቃል። የህወሓቶች ጥረት ህዝብ በስብሰባው እንዳይሳተፍና አማራጭ ሐሳብ እንዳይሰማ መከልከል ነበር። ህወሓት የሚሰጋው ዓረና እንዳይቃወመው ሳይሆን ህዝቡ ፖለቲካ አውቆ እንዳይቃወመው ነው።
    ይሄ ተንኮል ግን የህወሓት ዕድሜ ያራዝማል የሚል ግምት የለኝም።

    አና ጐሜዝ ስለተቃዋሚዎች የተሻለ የአቋም ለውጥ አላደረገችም”ዶ/ር መረራ ጉዲና

    Merera-Gudina
    ከአውሮፓ ህብረት የፓርላማ አባላት ተወካዮች ጋር ከተገናኙትና ውይይት ካደረጉት መካከል ዶ/ር መረራ ጉዲና አንዱ ናቸው፡፡ ዶ/ር መረራ ጉዲና በወቅቱ ስለነበረው ሁኔታ ከሎሚ አዘጋጅ ቶማስ አያሌው ጋ ያደረጉት ቆይታ እንደሚከተለው ቀርቧል፡- ሎሚ፡- ከአውሮፓ ህብረት ተወካዮች ጋር መገናኘታችሁና ውይይት ማድረገችሁ ይታወሳል፡፡ በወቅቱ የነበረውን አጠቃላይ ሁኔታ ቢገልፁልን;ይታወሳል፡፡ በወቅቱ የነበረውን አጠቃላይ ሁኔታ ቢገልፁልን; ዶ/ር መረራ፡- ጀአጠቃላይ ስለኢትዮጵያ ፖለቲካዊ ምህዳር፣ ከ1997 ዓ.ም. ምርጫ በኋላ የፖለቲካ ምህዳሩ አደገኛ በሆነ መንገድ እየጠበበ መምጣቱን፣ ነገሮች ወደኋላ መጓዛቸውን፣ መሠረታዊ የመንግስት ተቋማት የአንድ ፓርቲ ጉዳይ አስፈፃሚ መሆናቸውን፣ ፓርላማው፣ ምርጫ ቦርዱ፣ ሚዲያውም ሙሉ በሙሉ በሚባልበት መልኩ በአንድ ፓርቲ ስር መሆናቸውን ገልጸናል፡፡ሠላማዊ ሰልፎችን፣ ሕዝባዊ ስብሰባዎችን ማካሄድ ችግር እንደፈጠረብን፣ በሀገሪቱ ውስጥ ለመንቀሣቀስ ችግር እንደገጠመን በስፋት አስረድተናል፡፡ ስለእረኞች ጉዳይ በስፋት አንስተናል፡፡ ሉዊ ሚሼል የሚባለው የእርዳታ ሰጪ ኃላፊውና አንድ ሌላ ሰው እስረኞችን ገብተን እንድናይ ተፈቅዶልናል ሲሉ ገልፀውልናል፡፡ ፓርላማ ውስጥ ከተቃዋሚ ፓርቲዎች አንድ ተወካይ ብቻ መኖሩን ይገልፁ ነበር፡፡ ከ97 ምርጫ የተዘረፈው ተዘርፎ የተረፈው 170 መቀመጫ ነበረን፡፡ ይሄን በማነፃፀር ተገልፆላቸዋል፡፡ አጠቃላይ እንግዲህ ኢህአዴግ ዴሞክራሲያዊ ተቋማትም ሆነ ስርዓትን ለመገንባት ሀሣብ እንደሌለው ለማስረዳት ሞክረናል፡፡ ሎሚ፡- እናንተን ያናገሩት የአውሮፓ ህብረት ተወካዮች ምን ዓይነት አቋም ነበራቸው; ዶ/ር መረራ፡- በአጠቃላይ እኛን ለመስማት ነበር የጠሩን፡፡ እንዲያውም እኔን ጨምሮ አጥብቀን ያነሣነው ሀሳብ፣ ገንዘብ ስትሰጡ ስለ ሰብአዊ መብቶችና ሌሎች ጉዳዮች አታነሱም የሚል ነበር፡፡ ለእሱ ጥያቄ አንዱ የአውሮፓ ፓርላማ አባል እዚህ አዲስ አበባ ያለውን ተወካይ ጠየቀው፡፡ አንዷ የአውሮፓ ሕብረቱ ምክትል ተወካይ እሷም ከዚህ በኋላ አንዳንድ ነገሮችን እናደርጋለን ለማለት ሞክራ ነበር፡፡ እኛ ግን ከ1997 ዓ.ም. ምርጫ ወዲህ ትላልቅ የሚባሉት የአሜሪካ፣ እንግሊዝ፣ ፈረንሣይ ኤምባሲ ዲፕሎማቶች ተቃዋሚዎችን ሲሸሹ እንደነበር አስረድተናል፡፡ እኛ የምንለውን ነገር ነበር እነሱ በጥሞና ሲያዳምጡ የነበሩት፡፡ ሎሚ፡- ተቃዋሚዎች ምን ዓይነት እንቅስቃሴ እያደረጋችሁ ነው የሚል ሀሳብ አላነሱላችሁም; ዶ/ር መረራ፡- ጠይቀውናል፤ ምን እየሰራችሁ ነው? ምህዳሩ እንዴት ነው? እንዴት እየሰራችሁ ነው? ብለው ጠይቀውናል፤ መልሰንላቸዋል፡፡ ሎሚ፡- ምላሻችሁ ምን ነበር; ዶ/ር መረራ፡- ተቃዋሚዎች መስራት የምንችለውን እየሞከርን ነው ያለነው፡፡ የተቃዋሚ ህብረትም እንደ መድረክ ዓይነቱ ምን እየሞከረ እንደሆነ አስረድተናል፡፡ እነሱ የሚጠይቁን “ለምን አንድ አልሆናችሁም” ስለሆነ አንድ ለመሆን እየተሞከረ እንዳለ ለማስረዳት ሞክረናል፡፡ ሎሚ፡- የዛሬ ዘጠኝ አመት ወ/ሮ አና ጐሜዝን በደንብ ያውቋቸዋል፡፡ ከዘጠኝ አመት በኋላ እንደመገናኘታችሁ መጠን ምን አዲስ ነገር ተመልከታችሁ? ወ/ሮ አና ጐሜዝ በኢትዮጵያ ጉዳይ ያላቸው አቋም ምን ይመስላል; ዶ/ር መረራ፡- አና ጐሜዝ ከእኛ ተቃዋሚዎች የተሻለ የአቋም ለውጥ አላደረገችም፡፡ የዛን ጊዜም ምርጫ እንደተጭበረበረ ለማስረዳት ሞክራለች፡፡ አሁንም ቢሆን ተቃዋሚዎች ችግር ላይ እንደሆኑ የፖለቲካ ምህዳሩ እየጠበበ እንደሄደ ከሞላ ጐደል አስረድታለች፤ አዲስ አቋም ግን አላሣየችም፡፡ ድሮ የገፋችበትን አቋም አጠናክራ በኢትዮጵያ ዴሞክራሲያዊ ስርዓት ለመፍጠር የፖለቲካ ምህዳር መስፋት በዋናነት አስፈላጊ መሆኑን፣ በዚህ አቅጣጫ የአውሮፓ መንግስታትም መስራት እንዳለባቸው ገልፃለች፡፡ በ1997 ዓ.ም. ከነበራት አቋሟ የተለየ ለውጥ አላሣየችም፡፡ ሎሚ፡- ወ/ሮ አና ጐሜዝ “ጠ/ሚ መለስ ቢኖሩ ኖሮ ወደዚህ ሀገር አልገባም ነበር፡፡ ከዛም ባለፈ የጠ/ሚ መለስ አለመኖር ለውጥ ይፈጥራል” ብለው ተናግረዋል; ዶ/ር መረራ፡- ይሄንንም አንስተዋል፤ ለምሣሌ፡- ጠ/ሚ መለስ ቢኖር ወደዚህ አልመጣም ነበር፤ እናንተስ ጋ ምን ለውጥ አለ? ብለው ጠይቀውናል፡፡ እኛ ጋ ለውጥ ካለ ወደፊት ሣይሆን ወደኋላ የመሔድ ለውጥ ነው፡፡ የምርጫ ጉዳይ የፖለቲካ ምህዳር ጉዳይ፣ የመንግስት ተቋማት ጉዳይ፣ የሚዲያ ጉዳይ…ምንም ለውጥ የታየባቸው መስኮች እናዳልሆኑ አስረድተናል፡፡ ምንም የፖሊሲ ለውጥ እንዳላየን ለማስረዳት ሞክረናል፡፡ ሎሚ፡- እናንተን ካናገሩ በኋላ የመንግስት ባለስልጣናትን አናግረዋል; ዶ/ር መረራ፡- ይመስለኛል፡፡ ፈቃድም ስላገኙ፣ ከዛ በኋላም መልሰው ሊያናግሩ ይችላሉ፡፡ ያናገሩም ይመስለኛል፡፡ ለምሣሌ እስር ቤት (ቃሊቲን) ለማየት ፈቃድ ያገኙት ከዛ በፊት ነው፡፡ ሁለት የእኛ አመራሮች ፈቃድ አግኝተዋል ነው ያሉት፡፡ ከዛ በፊት እና በኋላ ማንን እንዳናገሩ አናውቅም፡፡ ግን የተወሰኑትን የመንግስት ባለስልጣናት ማናገራቸውን ከንግግራቸው መገመት ይቻላል፡፡ ሎሚ፡- ካደረጋችሁት ውይይት አንፃር ተቃዋሚ የፖለቲካ ድርጅቶች የሚጠይቁት ጥያቄ ሊኖር ይችላል፡፡ ከዚህ አንፃር መፍትሄ ሊያገኙ ይችላሉ; ዶ/ር መረራ፡- ይሔ በሁለት ዓይነት መልኩ የሚታይ ነው፡፡ እኛም የቤት ስራዎቻችንን መስራት የግድ ነው፡፡ የጋራ የፖለቲካ አጀንዳን በሰከነ መንገድ መግፋት፣ የተቃዋሚዎችን አቅም የመገንባቱ እነዚህ፣እነዚህን የቤት ስራዎች ካልሰራን ፈረንጆች ራሣቸው የረዷቸውን ሰዎች ነው የሚረዱት፡፡ እራሣችንን ካልረዳን እግዚአብሔር ይረዳናል፡፡ ፈረንጅ ይረዳናል ብለን መጠበቁ አያዋጣም፡፡ የቤት ስራዎቻችንን ለመስራት እንሞክራለን፤ እናንተም የቤት ስራዎቻችሁን ስሩ ነው ያልኩት፡፡ የኢትዮጵያ መንግስት ላይ ተገቢ ዲፕሎማሲያዊ ጫና አድርጉ፡፡ ገንዘቡን (ቼኩን) ስትሰጡ ዝም ብላችሁ ሣይሆን ይሄ ገንዘብ የት እየደረሰ መጠየቅ አለባችሁ፡፡ ለሕዝቡስ እየደረሰ ነው ወይ ብቻም ሣይሆን ከዛም አልፋችሁ፣ ስለእስረኞች ጉዳይ፣ ስለሰብዓዊ መብት ረገጣ ጉዳይ፣ ስለፖለቲካ መድሎ ጉዳይ፣ ነፃ ፍትሐዊ ምርጫ፣ ስለሚዲያ ጉዳይ ጠይቁ የሚሉ ነገሮችን አንስቻለሁ፡፡ እኛም የራሣችንን የቤት ስራ መስራት አለብን፡፡ እናንተም ደግሞ የቤት ስራዎቻችሁን መስራት አለባችሁ፤ ዝም ብላችሁ ብቻ ቼክ መፃፍ አይደለም የሚለውን በአጭሩ ቅልብጭ ባለ ቋንቋ ለመናገር ሞክረናል፡፡ ሎሚ፡- ወ/ሮ አና ጐሜዝ ስለ ጠ/ሚ መለስ የነገሯችሁን ለኢህአዴግ ባለስልጣናት የገለፁላቸው ይመስልዎታል; ዶ/ር መረራ፡- እርግጠኛ አይደለንም፡፡ ከአፈ-ጉባኤ አባዱላ ጋር የተነሣችሁን ፎቶ ሪፖርተር የተባለ የኢህአዴግን ልብ እያየ የሚፅፍ ጋዜጣ ላይ አይቻለሁ፡፡ ምን እንደተባባሉ አላውቅም፡፡ ምን እንደተባባሉ እነሱ ነው የሚያውቁት፡፡ አልጠየቅንምም፡፡ እንደአስፈላጊ ነገርም አላየሁትም፡፡ ሎሚ፡- ከእናንተ ጋር ውይይት ያደረገው የአውሮፓ ፓርላማ ቡድን ለኢትዮጵያ መንግስት/ኢህአዴግ ያለው ዕይታ ምን ዓይነት ነው; ዶ/ር መረራ፡- አውሮፓ ህብረትም ሆነ አሜሪካኖች ተቃዋሚዎች የኢህአዴግን መንግስት ከስልጣን ሊያወርዱ ይችላል ብለው ማመን አለባቸው፡፡ በዚህ ላይ እርግጠኛ አይደለሁም፡፡ ከነሱም ሆነ ከእነሱ ምሁራን ጋር ስንወያይ የተቃዋሚውን መከፋፈል ደጋግመው ያነሱታል፡፡ ያ በተዘዋዋሪም ሆነ በቀጥታ እናንተ ኢህአዴግን አንቃችሁ ከስልጣን ለማውረድ መዘጋጀት አለባችሁ የሚል ነው፡፡ ስለዚህ የእነሱን ወዳጅነትና ድጋፍ የምንሻውን ያክል የእሣራችን የቤት ስራዎች የመስራት ግዴታ አለብን፡፡ በእኔ በኩል በተገቢው መንገድና ደረጃ እየሰራን አይደለም የሚል አቋም አለኝ፡፡ ላለፉት 20 አመታት የኢህአዴግ ተቃዋሚዎች በሀገር ውስጥም ሆነ በውጭ የሚገኙ የቤት ስራዎችን መስራት አልቻሉም፡፡ የኢትዮጵያ ፖለቲካን ወደፊት የመሄድና ያለመሄድ የሚወሰነው እሱ ነው፡፡ የጋራ አጀንዳ ቀርፀን፣ ይህንን የጋራ አጀንዳ ገንብተን፣ አቅም በፈቀደ መንገድ የኢትዮጵያ ሕዝቦችን ይዘን ወደፊት መግፋት አለብን፡፡

    የግንቦት 7 ህዝባዊ ሃይል የተመሰረተበትን አንደኛ አመት አስመልክቶ የተሰጠ ድርጅታዊ መግለጫ


    December 17, 2013
    ታህሳስ 7  2006 ዓም የግንቦት 7 ህዝባዊ ሃይል ከተመሰረተ  አንድ አመት ሞላው። አንድ አመት  በጭንቅና  በአሳር  ለተያዘች የዛሬይቱ ኢትዮጵያና ህዝቧ እጅግ ረጅም ግዜ እንደሆነ ህዝባዊ ሃይሉ በሚገባ  ይገነዘባል። ባላፈው አንድ አመት ውስጥ የኢትዮጵያን ህዝብ የመከራ የአሳርና የውርደት ህይወት ይበልጥ እየሰፋ፣ የሚፈጸምበት ግፍ ይበልጥ እየገዘፈ መሄዱን አይተነዋል። በሃገርና በህዝብ ላይ እየወረደ ያለውን ወያኔ ወለድ የስቃይና የፍዳ ናዳ በቅጡ ላጤነው  ሃገሪቱና ህዝቧ የአዳዲስ የስቆቃና የመከራ አይነቶች መፈተኛ ቤተ ሙከራዎች እየተደረጉ ለመሆኑ ጥርጥር አይኖረውም። ለሚራበው ለሚረገጠው በግፍ ለታጎረው፣ በኑሮ ውድነት ለሚጠበሰው፣ ለተሰደደው ለተፈናቀለው ኢትዮጵያዊ እንድ አመት በሲኦል የቀናትና የወራት መቁጠሪያ እንደሚለካ ዘመን እጅግ የረዘመ የስቃይ ግዜ ነው።Ginbot 7 Popular Force logo
    የዋልድባ መነኩሳት ገዳማችን  አትድፈሩ አታፍረሱ በማለታቸው እየተገረፉ ለዘመናት ፈጣሪያቸውን ከሚማጸኑበት ለሃገርና  ለህዝብ ምልጃ ከቆሙበት ገዳም በዘር መመዘኛ እየተለዩ  እንደቆ ሻሻ ተጠርገው የተባረሩበት ፣ እምነታችን አትንኩ ያሉ የእስልምና እምነት ተከታዮችና  መሪዎቻቸው በሃሰት ክስ ተመስርቶባቸው  ወህኒ መውረዳቸው አንሶ  ወንድሞቻችን ይፈቱ በማለት  ሰላማዊ  ጥያቄ ያቀረቡ ወገኖቻቸን በወያኔ ነፍሰ- ገዳዮች  በአረመኔያዊ ጭካኔ የተጨፈጨፉት በዚሁ አመት ነው። ወያኔ በህዝብ መሃከል በዘራው የዘር መርዝ የተነሳ በሽዎች የሚቆጠሩ አማሮች ከጉራ ፈርዳና ከቤንሻንጉል፣ ኦሮሞዎች ለዘመናት ከኖሩበት ምስራቅ ሃረርጌ  አካባቢ  እንዲፈናቀሉና በገዛ ሃገራቸው መድረሻ ቢሶች  እንዲሆኑ የተደረገው በዚህ አንድ አመት ውስጥ ነው። ጋምቤላዎች ሙርሲዎች አፋሮችና ሌሎችም ብሄረሰቦችና ማህበረሰቦች የተጨፈጨፉበት፣በልማት ስም ለመጡ የውጭ ወራሪዎችና ወያኔ ለፈጠራቸው ቱጃሮች ቦታ እንዲለቁ ተደርጎ ቀደምቶቻቸው ለዘመናት ከኖሩባቸው ቀየዎች እንዲነቀሉ ተደርገው እንደ አልባሌ ነገር የትም እንዲበተኑ የማድረጉ ሂደት ከመቼውም በላይ ተጠናክሮ የቀጠለው በዚሁ አመት ነው። በዚሁ አንድ አመት በወያኔ የሃገሪቱ ገዥዎች በህዝብ ላይ የተፈጸመው  ጭካኔና ወንጀል ተዘርዝሮ  የሚያልቅ አይደለም።
    ይህ ወያኔ  ሰራሽ ሃገር በቀል የውርደትና  የስቃይ ህይወት አልበቃ  ብሎ ወያኔ ከሳውዲ የጨለማ ዘመን ገዥዎች ጋር በመተባበር ወንድሞቻችን በሳውዲ አውራ ጎዳናዎች ላይ እንዲታረዱ እህቶቻችን በቡድን በተደራጁ የሳውዲ ጎረምሳዎች  እንዲደፈሩ ሁኔታዎችን አመቻችቶ  ለኢትዮጵያውያን ያለውን እጅግ የከረረ ጥላቻ በአደባባይ ያሳየበት አመት ነው። እንዲህ አይነቱ የጅምላ ግፍና  ውርደት ከመከሰቱ በፊት ህዝባዊ ሃይሉ በአረብ ሃገር በባርነትና  በስደት የሚገኙ እህትቶቻችንን ወንድሞችችን ስቃይ  ስቃዩ አድርጎ በመውሰድ “ላንቺ ነው” በሚለው ድርጅታዊ መዝሙሩ “በባለጌ  አረቦች መዳፍ ውድ ክብራቸው ለጎደፈው እህቶቻችን፣ በአረቦች የባርነት ቀንበር ጀርባቸው ለጎበጠው  ወገኖቻችን እንደርስላችኋለን፣ የተሰባሰብነው  ደማችን የሚፈሰው የመከራ ቀናችሁን ለማሳጠር ነው” የሚል ቃል ኪዳኑ ሰጥቶ  ነበር። የድርጅታችንን ምስረታ አንደኛ  አመት ስናከብር ልባችንን ደስታ ሳይሆን ሃዘን እንዲሞላ የሚያደርገው ይህ ቃል ኪዳናችን ለማክበር የጀመርነው ጉዞ ከድርጅት ምስረታና ከድርጅታዊ ዝግጅት አልፎ   በኢትዮጵያ ህዝብ ጥላቻና ንቀት  የተነፋውን የወያኔን እብሪት በማስተንፈስ የወሰዳቸው ተጨባጭ የአለኝታነት እርምጃዎች ባለመኖራቸው ነው።
    ምንም እንኳን ግንቦት7 ህዝባዊ ሃይል እራሱን እንደ ድርጅት አቁሞ  ኢትዮጵያውያንን አሰባስቦ  መራራው ትግል የሚጠይቀውን የፖለቲካ  የወታደራዊ ስልጠናና ትጥቅ አስታጥቆ  በወያኔ  ላይ ለመዝመት የጀመረውን ጉዞ የሚያስቆመው ምድራዊ ሃይል እንደሌለ ብናውቅም የህዝብ ስቃይ ለግዜው መቀጠሉ የህባዊ ሃይሉን አባላት ማሰቃየቱ አልቀረም። በወያኔ  ግፈኛ አገዛዝ የተንገፈገፈው ወገናችን ህዝባዊ ሃይሉ የወያኔን አገዛዝ እድሜ  የሚያሳጥሩ ፈጣን እርምጃዎችን እንዲወስድ በከፍተኛ  ጉጉት እየተጠባበቀ እንደሆነ  እናውቃለን። ህዝባዊ ሃይሉን ለመቀላቀል በመቶ ሽዎች የሚቆጠሩ የሃገሪቱ ዜጎች በተጠንቀቅ እንደቆሙ እናውቃለን። እነዚህ ዜጎች ከሁሉም የእምነት የቋንቋ  የጾታ የእድሜ  የኑሮና  የማህበረሰብ ስብጥር የሚያካተቱ  እንደሆኑ እናውቃለን። በሃገሪቱ ታሪክ ተሰምቶና  ታይቶ በማይታወቅ ደረጃ  የወታደር ልብሱን  እየጣፈ እንዲለብስ፣  የወታደር ጫማውን መቀየሪያ አጥቶ  ሸበጥ እንዲያደርግ የተገደደውን፣  የወያኔ ጀነራሎች በስልጣንና  በዘረፋ ሲያብጡ በድህነት እንዲሟሽሽ የተፈረደበት የሃገሪቱ ሰራዊት በዘር በእምነት ሳይለያይ ከህዝባዊ ሃይሉ ጎን ለመቆም አሰፍስፎ  የቆመ  እንደሆነ  እናውቃለን። ይህ ሃገራዊ እውነታ ለህዝብ የገባነውን ቃልኪዳን የለምንም ጥርጣሬ  ማስከበር እንደምንችል በሙሉ ድፍረት እንድናውጅ የሚያስችለን ሃቅ ነው።
    የወያኔ ጀንበር እየጠለቀች የኢትዮጵያ  ህዝብ ጀንበር እየፈካች የመሄዱ ጉዳይ እንደማይታጠፈው  የመንጋትና  የመምሸት የተፈጥሮ ህግ ነቅነቅ የማይል እንደሆነ ግንቦት7 ጠንቅቆ ያውቃል።  እውቀታችን ልዩ ጥበብ የሚጠይቅ ኣይደለም። ግፍ ፍትህን አሸንፎ፣ እውነት በሃሰት ተደፍቃ፣ ጥላቻ ፍቅርን፣ አድሎ እኩልነትን፣ ሃገራዊ ክህደት ሃገር መውደድን፣ ባንዳነት አርበኛናትን ለዘላላሙ ቀብረው የሄዱበት የሃገራችንና  የሰው ልጆች ታሪክ የለምና የወያኔን አይቀሬ ሞት ለመተንበይ  ልዩ ጥበብ አያሻንም። ይህን እኛ ብቻ ሳንሆን በዘረፋና በጥላቻ  የደነዘዘ ህሊና ያዳበሩት የወያኔ  ባለስልጣናትም ያውቁታል። ያለእኔ  ጀግና የለም፣ ያለእኔ  አልሞ  ተኳሽ የለም በሚል እብሪት በመጻደቅ የሚታወቁት ወያኔዎች በመቶ ሽዎች በሚቆጠሩ ወታደሮች ተከበው፣  በታንክ በአይሮፕላን በሚሳይል ታጅበው ከሚኖሩበት ቤተመንግስትና ቪላዎች ውስጥ ብርክ እንዲይዛቸው ያደረገው ለመሆኑ፣  ሳር ቅጠሉ ግንቦት ሰባት እየመሰላቸው ሲበረግጉ እንደሚያመሹ፣  የግንቦት ሰባት አባላት እያሉ ከድርጅታችን ጋር አንዳችም ግንኙነት የሌላቸውን ዜጎች እያሰሩ ሲያሰቃዩ ፣  ከምላሳቸው ላይ ግንቦት 7  የሚል ስም ተፈናጦባቸው  እንደሚውሉ በራሳቸው ሚድያ  ወያኔዎች ራሳቸው እያሳዩን እያስደመጡን ነው። ከዚህም አልፎ በዚህ አንድ አመት ውስጥ  የህዝባዊ ሃይሉን መሪዎች በመግደል ድርጅቱን ለማኮላሸት ይቻላል በሚል ወያኔ የላካቸው ነፍሰ ገዳዮችና ድርጅቱን ከውስጥ ለመቦርቦር ያሰማራቸው ሰርጎገቦች ተራ በተራ ተልእኳቸው እየከሸፈ በህዝባዊ ሃይሉ እጅ እየወደቁ ወይም ተልእኳቸው እንደማይሳካ ሲረዱ እየፈረጠጡ ወደ ወያኔ ሲመለሱ አይተናል።
    ያለፈው አንድ አመት ተመክሯችን ስለወያኔ  ብቻ ሳይሆን ስለራሳችንም ጥንካሬና  ድክመት ብዙ ነገሮች ያስተማረን ኣመት ነው። የቀደምቶቻችን የጀግንነት የአርበኛነት ቅርስ በመላ ህዋሳቸው የተሸከሙ  ለኢትዮጵያ እና  ለህዝቧ ሲሉ ደማቸው ለማፍሰስ ውድ ህይወታቸውን ለመሰዋት ወደኋላ የማይሉ ቆራጥ ብቻ ሳይሆኑ አርቀው የሚያዩ  በርካታ ልጆች  ሃጋሪቷ ያሏት መሆኑን ያረጋገጥንበት አመት  ነው።  በሌላ በኩል ደግሞ  ድርጅታችን የኢትዮጵያን ህዝብ ብቸኛው የመንግስት ስልጣን ባላቤት የማድረጉን ታሪካዊ ራእዩን ለመሳካት የሚያደረገው ትግል ከወያኔ ጋር ብቻ ሳይሆን ከራሳችንም ጋር የሚደረግ እንደሆነ  በሚገባ  የተረዳነው  በዚሁ የአንድ አመት የድርጅታችን እድሜ  ነው። ከራሳችን ጋር የሚደረግ ትግል ወያኔ በማህበረሰባችን ውስጥ ከዘራቸውና የሃገሪቱን ዜጎች እንዲበክሉ ካደረጋቸው የዘረኛነት የአድሎ  ከህዝብና  ከሃገር ጥቅም በፊት የራስን ጥቅም ማስቀደም፣ የሱሰኛነትና የሙስናና ሌሎችም አደገኛ ባህሎች ጋር ነው።
    ህዝባዊ ሃይሉ ደግሞ  ደጋግሞ  እንደገለጸው ትግላችን አንድ መንግስታዊ ስርአት ወድቆ ሌላው የመንግስት ስርአት በመጣ ቁጥር የህዝብ ተስፋ እየጨለመ  “አዲስ ከመጣው ስርአት ያላፈው ያረጀ ስርአት በግፈኛነቱ በዘራፊነቱ ያነሰ ነበር” የሚል የግፈኛና የዘራፊ ስርአቶች ንጽጽር ላይ የቆመ አሳዛኝ የህዝብ ህይወት እንዲያበቃ ነው። ደርግን ያየ የአጼውን ስርአት እንከኖች ረስቶ ንጉሱ ይሻሉን ነበር ያለበት፣ ወያኔን ያየ የደርግን አስከፊ ዘመን ረስቶ መንጌ በስንት ጣሙ ያለበት አሳዛኝ ሁኔታ ከወያኔ መውደቅ በኋላ በሃገራችን እንዳይደገም ነው ትግላችን። የኢትዮጵያ ህዝብ የውድ ልጆቹን ህይወት ገብሮ ወያኔን በማስወገድ የሚያመጣው ስርአት ከወያኔ ብሶ ህዝብ ወያኔ ማረኝ የሚልበትን ቅስም ሰባሪና አዋራጅ የታሪክ ቅጥልጥሎሽ  እንዳይቀጥል ማድረግ ህዝባዊ ሃይሉ የተመሰረተበት፣ አባላቱ መከራ ለመቀበልና መስዋእትነት ለመክፈል በረሃ የገቡበት ዋናውና ብቸናው ምክንያት ነው። ትግላችንን መራራ የሚያደርገው ከበሰበሰውና የአንድ ጀምበር የህዝብ ቁጣ ከታሪክ ቆሻሻ የመጠያ ስፍራ ከሚከምረው  የወያኔ ስርአት ጋር ብቻ ሳይሆን በወያኔ ቦታ የሚተካውን ስርአት ከአድሎና ከዘረኛነት ከዘረፋና ሃገራዊ ክህደት የጸዳ፣ ዳግም ለኢትዮጵያውያን ውርደትና እንግልት ምክንያት እንዳይሆን ለማድረግ ከራሳችን ጋር ሳይቀር የማያቋርጥ ትግልን ማድረግ የግድ ስለሚል ነው። ህዝባዊ ሃይሉ የአመጽ ትግል የሚያደርግ፣ የመሳሪያው ብዛትና  የሰራዊቱ ቁጥር እያደገ  የሚሄድ ሃይል መሆኑን ስለምንረዳ  ይህን ሃይል ገና ከጅምሩ ከብዙ እንከኖች እያጸዱ ማደራጀት ካልተቻለ  በሃገርና በህዝብ ላይ የሚመጣውን አደጋ  የህዝባዊ ሃይሉ አባላት ጠንቅቀው የተረዱት ሃቅ ነው። ይህ ግንዛቤ የሰራዊቱን አባላት በጥንቃቄ መመልመልን፣ ማሰልጠንንና መገንባትን የግድ የሚል ነው።
    ይህ ከራሳችን ጋር የሚደረግ ትግል እጅግ መራራ ነው። ታሪካዊ ስህተቶችን ላለመድገም የሚደረግ ትግል ነው። ይህ ትግል የአካልና የመንፈስ ጽናትን፣ ሃቀኛነትን፣ ታማኝነትን፣ ጀግንነትን የሚጠይቅ ትግል ነው። የወያኔ ስርአት ከሃገር ግድያው በተጨማሪ ትውልድን ለመግደል ሆን ብሎ ያስፋፋቸው እኩይና ጎጂ ባህሎችና ልምዶች ምን ያህል ማህበረሰባችንን እንደጎዱት ህዝባዊ ሃይሉ ባላፈው አንድ አመት እድሜው በሚገባ የተረዳው ጉዳይ ሆኗል። ህዝባዊ ሃይሉ የሚመኘውን የኢትዮጵያ ትንሳኤና ተሃድሶ እውን ለማድረግ እነኝህ  ወያኔ ሆን ብሎ  ያስፋፋቸውን የባህልና የሞራል ብክለት ማጽዳት የግድ እንደሆነ የተረዳ አካል ሆኗል።
    ትግላችን መደፍረስን መጥራትን፣ መንተክተክን መስከንን የትግሉ ሂደት አካል አድርጎ  የሚጓዝ ነው።   ትግሉ የሚልመጠመጠውን እንደቀስት ቀጥ ብሎ ከሚራመደው፣ በካፊያው የሚንቀጠ ቀጠውን ለዶፉ ደንታ ከሌለው፣ ዝናር በቅፌን ከምሩ ተኳሽ  የሚለይ መራራ ትግል ነው። ያለፈው አንድ አመት ይህን አስተምሮናል። ህዝባዊ ሃይሉ ትግሉ ቀላል ነው የሚል ከእውነታ ጋር ያልተያያዘ ቃል ለህዝብም ሆነ ህዝባዊ ሃይሉን ሊቀላቀሉት ለተዘጋጁት ወገኖቹ አይናገርም። ህዝባዊ ሃይሉን ለመቀላቀል ለተሰለፉ በሽዎች ለሚቆጠሩ ወገኖቻችን ትግሉ የሚጠየቅውን የሞራል የስብእና ጥብቅነት፣ከፍተኛ  የሃገርና የወገን ፍቅር፣ ጥልቅ የሆነ የመስዋእትነት ፈቃደኛነት የሚጠይቅ መሆኑን ከማስረዳት አንቦዝንም። ህዝባዊ ሃይሉ ለህዝብ ቃል እንደገባው ከወያኔ  ጋር የምናደርገው ትግል በጥበብ በእውቀት በጥናት በጥንቃቄ የምናደርገደው ነው። ነጻነት ያለመስዋእትነት እንደማይሳካ ብናውቅም ለተራ የፕሮፓጋንዳ ፍጆታ ስንል በቂ ዝግጅት ያልተደረገበት የሃገሪቱን ውድ ልጆች በከንቱ የሚማግድ ጀብደኛ እንቅስቃሴ  አናደርግም። የውሸት ተስፋ  ህዝብን አንመግብም።  አይናችንን ከዋናው የኢትዮጵያና  የህዝቧ  ጠላት ከሆነው ከወያኔ ላይ አንስተን በሌሎች  ወያኔን እቃወማለሁ በሚሉ ሃይሎች ላይ አንተክልም። ከወያኔ ሌላ ወደ ጎን የምንዋጋው፣ የምንጨቃጨው አታካራ የምንገጥመው ምንም ሃይል አይኖርም። ወያኔን ለመምታት ህዝባዊ ሃይሉ የጨበጠው  ቡጢ ወገኖቻችን በፍቅር ለመጨበጥ የሚዘረጉ ጣቶች  እንዳሉት በጸረ ወያኔ ዴሞክራሲያዊ ትግሉ  ከልባቸው ለመተባበር ለሚፈልጉ ሃይሎች ሁሉ ግልጽ እናደርጋለን።
    ያለፈው አንድ አመት የመሰባሰብ የድርጅት ምስረታ  መሰረታዊ የሆኑ የፖለቲካና የወታደራዊ  ስልጠና የተሰጠበት፣ የድርጅት ማጠናከሪያና የማጥራት ሂደት የተካሄደበት ነው። በዚህ ረገድ የተሰራው ስራ አጥጋቢ ውጤት አስገኝቷል። ስልጠናው፣ ድርጅት ማጠናከሩና  ማጥራቱ ወደፊትም የሚቀጥል ነው። መጪውን አመት የተለየ የሚያደርገው ህዝባዊ ሃይሉ በህዝብ ላይ በሚደርሰው ግፍና ውርደት ከሚሰማው ከፍተኛ ብስጭትና ቁጭት አልፎ ባላፈው አመት ሊደርስላቸው ያልቻለውን የሃገራችንን ግፉአን ህዝቦች መታደግ የሚችልበትን እርምጃዎች መውሰድ የሚችልበት አመት መሆኑ ነው። በዚህ የህዝባዊ ሃይላችን የአንደኛ አመት ምስረታ  ክብረ በአል ወቅት ወገንም ጠላትም በግልጽ እንዲያውቀው የምንፈልገው ይህን ሃቅ ብቻ ነው።
    ውድመት ለዋናውና  ለብቸኛው የኢትዮጵያ ህዝብና  የኢትዮጵያችን ጠላት ለሆነው የወያኔ ገዥ ጉጅሌ!
    ድል በወያኔ ግፈኛ ስርአት አበሳውን ለሚያየው የመላው የኢትዮጵያ  ህዝብ!
    የግንቦት 7 ሕዝባዊ ኃይል
    Ginbot 7 Popular Force
    www.ginbot7pf.org
    Tel: +44 208 123 0056
    email: pr@ginbot7pf.org

    Monday, December 16, 2013

    ነጋሪቱም ተጎስሟል፤ፋኖም ተሠማርቷል !!!


    ዛሬ ኢትዮጵያዊያን እያዩ ያሉት ውርደት ቃል የሚገልፀው አልሆነም። ኢትዮጵያ በታሪኳ ዛሬ እየደረሰ ያለ ዓይነት ውርደት ደርሶባት እንደሆነ በታሪክ የተመዘገበ ነገርም ተፈልጎ አልተገኘም። ይሄ ለኢትዮጵያዊያን የጨለማ ዘመን ነው። በኢትዮጵያ እንዲህ ስደትና እንግልት፤ ሃዘንና ዋይታ የበዛበት ዘመን ታይቶ አይታወቅም።
    በዚህ ግዜ በኢትዮጵያችን መንግስት ነኝ እያለ ራሱን የሚጠራ ቡድን አለ።ይሄ ቡድን አገሪቷን ከተቆጣጠረ ዘመን ጀምሮ ኢትዮጵያ የገባችበት የውርደት አዘቅት ከባድ ነው። ኢትዮጵያ ውስጥ በህወሃቶች አዝማችነት ተስምቶ የማይታወቅ ጆሮን ጭው የሚያደርግ ግፍ በዜጎች ላይ ይፈፀማል። የተለየ የፖለቲካ አመለካከት ያላቸውን ሰዎች ይዘው ግብረ ሶዶም እንዲፈፀምባቸው ያደርጋሉ፤ ሴቶች ልጆችን በጋራ ሁነው ይደፍራሉ፤ በተቀደሱ ስፍራዎች ገብተው ቅዱሱን ስፍራ ያረክሳሉ፤ ዜጎችን ከእርሻ ማሳቸው አፈናቅለው በገዛ አገራቸው መፃተኛ ያደርጓቸዋል። በአጠቃላይ ዜጎች በአገራቸው ተስፋ አጥተው ሃዘንተኛ እንዲሆኑ ያደርጋሉ። ተስፋ የቆረጡ ዜጎች ኢትዮጵያ ውስጥ ከምኖር ሂጄ ብሞት ይሻለኛል ብለው እግራቸው በመራቸው መንገድ ይሰደዳሉ። በእንዲህ ሁኔታ ከኢትዮጵያ በየዓመቱ ከ250ሺህ በላይ ወጣቶች ይሰደዳሉ።ገሚሱ በየበርሃው በውሃ ጥማት ወድቆ ይቀራል፤ ገሚሱም የባህር አዞ ቀለብ ሁኖ ዱካው ይጠፋል። ከሞት ተርፈው በየአርብ አገራቱ የደረሱ ዜጎች በሰው ልጆች ላይ ሊደርስ የማይገባ ወንጀል ይፈፀምባቸዋል።ባንዲራቸውን በአንገታቸው እንደጠመጠሙ ሬሳቸው ሜዳ ላይ ተጥሎ የአርብ መሳቂያ መሳለቂያ ይሆናሉ። በዚህ ሰሞን በሳውዲ ዓረቢያ እየተፈፀመ ያለው ግፍ ለኢትዮጵያዊያን ትልቅ ብሄራዊ ውርደት ሁኗል።
    ይሄ በእንዲህ እንዳለ “መንግስት ነኝ “ እያለ ራሱን የሚጠራው ህወሃት በዜጎቹ ሲቃና መከራ እየቀለደ ይገኛል።አንድ ግዜ ዜጎቼን እያወጣሁ ነው ይላል፤ ሌላ ግዜ ደግሞ የሥራ ፈቃድ የሌላቸው ስለሆኑ አላውቃቸውም ይላል። ህወሃቶች በዚህ ብቻ አላበቁም በኢትዮጵያዊያኑ ላይ እየተፈፀመ ያለውን ግፍ ለማስቆም አዲስ አበባ በሚገኘው በሳውዲ እምባሲ ፊት ለፊት ሠላማዊ ሠልፍ እንዳይደረግ መከልከል ብቻ ሳይሆን ለሠላማዊ ሰልፍ የወጡ ዜጎችን የቻሉትን ያክል ወደ እስር ቤት አግዘዋል፤ ያገኙትን ሁሉ በቆመጥ እንዲደበደቡ አድርገዋል። የአካል ጉዳትም አድርሰዋል። ይሄን ሁሉ ግፍ የሚታደግ፤የህዝቡንም ሮሮ የሚሳማ መንግስታዊ አካል አልተገኘም። ዓለምም ፊቷን ያዞረችብን የሚመስል ሁኔታ ታይቷል።
    ኢትዮጵያዊያን ቀና ብለን በኩራት በአርብ አገራት ጎዳናዎች ላይ የምንመላለስ ዜግች ነበርን። ስማችን ያማረ፤ ማንነታችን የተከበርን ዜጎች ነበርን። አረብ የሚያከብረን እንጂ እንዲህ የሚንቀንና የሚያዋርደን ዜጎች አልነበርንም። በዘመነ ህወሃት ግን ያ ሁሉ ክብራችን ተዋርዶ ዜጎቻችን እንደ ሌጦና ቆዳ በገንዘብ የሚሸጡ ሆኑ። በኢትዮጵያችን ላይ የነበሩ የቀድሞው ገዥዎች ምንም እንኳ ጨቋኞች ቢሆኑም ዜጎቻቸው በሌላ በማንም እጅ እንዲገላቱና እንዲዋረዱ የሚፈቅዱ አልነበሩም።በአንድ ወቅት አፄ ኃ/ስላሴን” ሠራተኛ ይላኩልኝ” ብለው የሳውዲው ንጉስ ሲጠይቋቸው “ለመሆኑ ምንድ ነው የምትፈልጉት መሃንዲስ ነው ወይስ ሃኪም “ብለው ይጠይቋቸዋል። አይ “እኛ የምንፈልገው በቤት ሠራተኛነት የሚያገለግሉንን ነው” ይላሉ አረቦቹ።አይ “እኛ ለቤት ሠራተኛ የሚሆን ዜጋ የለንም” ብለው መለስውላቸዋል።ለራሱም ሆነ ለወገኑ ክብር ያለው መሪ መልሱ እንዲህ እንጂ ሳውዲ ድረስ ሂዶ ዜጎቹን ለባርነት ለመሸጥ ሲዋዋል አይገኝም።
    ደሳለኝ ኃ/ማሪያም ከስድስት ወር በፊት ሳውዲ ድረስ ገስግሶ ሂዶ የቤት ሠራተኞችን ለአረቦቹ ለመላክ ተዋውሎ መመለሱ የሚታወስ ነው። ይሄን ውል ሲዋዋል ግን ስለ ክፍያ፤ ስለ ዕረፍት ግዜ፤ በህመም ግዜ ምን ይሆናል የሚሉ መሠረታዊ ቁም ነገሮች በውሉ ውስጥ አልተካተቱም። በእነዚህ ነገሮች ምክንያት የኢንዶኔዥያ እና የፊሊፕልንስ መንግስታት ግን ምንም እንኳ ድሃ ብንሆንም ዜጎቻችንን የምንሰደው የታወቀ የክፍያ መጠን፤ የእረፍት ግዜ፤ የህመም ፈቃድ እነዚህንና ሌሎችን መሠረዊ ሁኔታዎችን በተመለከተ የተሟላ የህግ ድንጋጌ ሲኖራችሁ ነው። ይህን ህግ እስከምታበጁ ዜጎቻችን የእናንተ መጫወቻ እንዲሆኑ አንልክም ብለው እምቢ ማለታቸው ይታወቃል። ህወሃት መራሹ መንግስት ግን ስለውጪ አገር አኗኗር ምንም ዓይነት ግንዛቤ የሌላቸውን ወጣት ልጆችን ያለ ምንም ህግ ከለላ አሳልፎ ለባእዳን ይሰጣል። ወጣት ሴቶችንና ወንዶችን ለግርድናና ለአሸከርነት የመላኩ የድለላ ሥራም ህወሃቶች ባቋቋማቸው ድርጅቶች ተካሂዶ ከዚህ ንግድ በተገኘው ገንዘብ ህውሃቶች ብዙ ገንዘብ አፈሱ። ወገኖቻችን ግን በአረቦች እጅ እንባቸውን በመዳፋቸው የሚሰፍሩ ሆነው ቀሩ።
    ለዚህ ሁሉ መከራ እና ውርደት ያበቃን ምንድ ነው የሚል ርዕስም የሰሞኑ የመወያያ ርዕስ ሆኗል። የመከራውና የውርደቱ ምንጭ ፈርጀ ብዙ ቢሆንም ህወሃት ዋነኛው የችግሩ ምንጭ ስለመሆኑ ብዙ ማስረጃዎችን ማቅረብ ይቻላል። በአጠቃላይ ግን ህወሃት መንግስት ነኝ ብሎ ሲያበቃ ዜጎችን ለመታደግ ምንም ዓይነት ተግባራዊ እንቅስቃሴ አለማድረጉ ብቻ ሳይሆን ዜጎች በሰላማዊ ሰልፍ እንኳ ቁጣቸውን እንዳይገልጹ መከልከሉ ማንነቱን ቁልጭ አድርጎ የሚያሳይ ነው።ለዚህ ብሄራዊ ውርደትና መከራ በመጀመሪያ ደረጃ ሊጠየቅ የሚገባው ህወሃት እንጂ ሌላ ማንም አይደለም። ህወሃት የኢትዮጵያዊያን ጠላት መሆንን የመረጠ የጠባብ ዘረኞች ቡድን ነው። ዜጎቻቸን እንዲህ ላለው ጉስቁልናና ውርደት እንዲጋለጡ ያደረጋቸው ህወሃት መሆኑን መያዝ ለነፃነት ለሚደረገው ትግል አንዱ አካል ነው።
    የተከበራችሁ ወገኖቻችን፤
    በሳውዲ አረቢያ የሚሰቃዩ ዜጎችን በተመለከተ ህወሃቶች ምንም ተቆርቋሪነት ያሳዩበት ሁኔታ እንዳልታየ ታውቃላችሁ።ለወገን ተቆርቋሪነት ከህወሃቶች የሚጠበቅ ስላልሆነ እኛ አንደነቅም። አስቀድመው በገንዘብ አሳልፈው ለሸጧቸው ዜጎች ይቆረቆራሉ ብሎ መጠበቅ የህወሃቶችን ባህሪይ ካለመረዳት የሚመነጭ ብቻ ሳይሆን ህወሃቶች ዜጎች ማኩረፊያ አገር እንኳን እንዳይኖሯቸው የሚያሴሩትን ሴራ ለመረዳት ካለመፈለግ የሚመነጭም ጭምር ነው። ወደ አረብ አገር የተሰደዱም ሆኑ በሌሎች አገር በስደት ላይ ያሉ ዜጎች በከፋቸው ግዜ ተመልሰው የሚገቡበት ሥፍራ አላቸው ለማለት የሚያስደፍር ሁኔታ በኢትዮጵያ የለም። ጉራፈርዳ እና ቤንሻንጉል አገርህ አይደለም ተብሎ የተባረረ ወጣት መግቢያው የት ነው ? ከዚህ ሥፍራ ወደ ሳውዲ የተሰደደ ወጣት መመለሻው ወደየት ነው ? በዚያች አገር ድንጋይ ለመፍለጥ እንኳ የኢሕአዴግ አባል እንዲሆን በሚገደድበት አገር ምን አገር አለኝ ብሎ ነው የከፋው ወደ ኢትዮጵያ የሚመለሰው? አዎን ኢትዮጵያዊያን ማኩረፊያ አገር የሌለን ከርታታ ዜጎች እንድንሆን ተደርገናል።አገር ያሳጡንም ህወሃቶች ናቸው እንጂ ሌላ ማንም አይደለም።
    እንግዲህ ምን ይደረግ?
    ይሄ ጥያቄ ግልጽና ቀላል መልስ አለው።አምርሮ መነሳት። ህወሃቶች በአዲስ አበባ ላይ ወንድ ልጅን አስገድደው ግብረ ሶዶም እንዲፈፀምበት ሲያደርጉ ሰምቶ “እነዚህ ምን ዓይነት አረመኔዎች ናቸው” ማለት ብቻ በቂ አይደለም።ለአረመኔ የሚገባውን ቅጣት ለመስጠት የአያቶቻችንን ጋሻና ጦር ማንሳት ግዜው የሚጠይቀው ታሪካዊ ግዴታ ነው። በሳውዲ አረቢያ በወገኖቻችን ላይ እየተፈፀመ የቆየውን ውርደት እንምባ ብቻ የሚያስቆመው አይሆንም። እንዲህ የአረብ መቀለጃ የሆነውን ማንነታችንና ክብራችንን አስመልሰን አንገታችንን ቀና አድርገን በአርብ ጎዳናዎች ላይ እንደቀድሞው ዘመን በኩራት እንድንመላለስ የአያቶቻችንን ትጥቅ ከተሰቀለበት አውርደን መታጠቅ ግዴታችን ሁኗል።
    ግንቦት ሰባት ንቅናቄ ውስጥ ያለን ኢትዮጵያዊያን በወገኖቻችን ላይ እየተፈፀመ ያለው ውርደት ብሄራዊ ውርደት ነው እንላለን። ከዚህ በላይ ሌላ ብሄራዊ ውርደት የለም። ለዚህ ውርደት ያደረሰንም ህውሃት ነው። ህወሃት እስካለ ድረስ ብሄራዊ ውርደታችን ይቀጥላል እንጂ አይሻሻልም። እኛ የሚደርስብንን ውርደት ለማስቆም አምርረን ተነስተናል። እኛ እንዲህ ተዋርደን መኖርን ከቅድሞዎቹ ኩሩዎች አያቶቻችን አልተማርንም።እኛን ባንዳዎችና የባንዳ ልጆች ህወሃቶች አንገታችንን አስደፍተው አዋርደው አይገዙንም። አያቶቻችን ለነፃነታቸው እና ለአገራቸው ክብር ሲሉ በቆሙበት በጀግኖች ሥፍራ ለመቆም መንገዱን ጀምረናል። ከእንግዲህ ወዲያ ከዚህ ጉዞ የሚያቆመን ምንም ዓይነት ምድራዊ ኃይል የለም። ለእኛ ነጋሪት ከተጎሰመ ቆይቷል እኛ የነጋሪቱን ድምፅ በሰማን ግዜ ሳናቅማማ ተነስተናል።
    እናንተስ ሳትቅማሙ ለመነሳት የነጋሪቱን ድምፅ ሰምታችኋል ? ከወደ ሳውዲ የተሰማው ያ የሲቃ ጩኸት፤ ያ ሮሮ፤ ያ እንምባ አስደንጋጩ የነጋሪት ድምፅ ነው። ከዚህ ድምፅ በኋላ ፋኖ ይሠማራል እንጂ አያለቅስም።ማልቀስ የናቁንና ያዋረዱን እንዲያከብሩን አያደርግም። ነጋሪቱ ከተጎሰመ በኋላ አገሬን፤ ክብሬን የሚል ተነስቶ ያያቶቹን ጋሻና ጦር ያነሳል እንጂ እንዲያው ዝም ብሎ አያጉረመርምም።አገር ተዋርዳ፤ ህዝብ ተበደሎ ዝም ብሎ ተንጋሎ የሚተኛ ካለ ይህን ብሄራዊ ውርደት ካመጡ ቡድኖች በምን እንደሚለይ ራሱን ይጠይቅ። አበቃን።
    ድል ለኢትዮጵያ ህዝብ !!!!

    Wednesday, December 11, 2013

    አንዱዓለም አራጌ ከእስር ቤት “እኔ እስሩ አልከበደኝም፤ በጣም ያሳዘነኝ ግን በኔ መታሰር ልትጠቀሙበት አልቻላችሁም” አለ

    (ዘ-ሐበሻ) የ2005 ዓ.ም የዘ-ሐበሻ አንባቢዎች ምርጥ ተብሎ የተሰየመውና በቃሊቲ ማረሚያ ቤት ዕድሜ ልክ እስራት ተፈርዶበት የሚገኘው ወጣቱ ታጋይ አንዱዓለም አራጌ እስር ቤት ሊጠይቁት ለሄዱት የተቃዋሚ ፓርቲ መሪዎች መልዕክት አስተላለፈ። በጣም ማዘኑንም ገለጸ።

    ዕድሜ ልክ እስራቱን ተቀብሎ እስር ቤት የሚገኘው አንዷለም አራጌ “ይቅርታ አልጠይቅም” በሚል እስካሁን በእስር ቤት እየማቀቀ ሲሆን “በእኔ መታሰር ብዙ ልትጠቀሙበት ስትችሉ አለመጠቀማችሁ ያሳዝነኛል:: እኔ አሁን በእስር ባለሁበት ሰዓት የኢትዮጵያን ሕዝብ የነፃነት ትግሉን ወደ ፊት ለመግፋት አጋጣሚ ሊሆንላችሁ ቢችልም አልተጠቀማችሁበትም ” ሲል የተቃዋሚ ፓርቲ መሪዎችን መውቀሱን የዘ-ሐበሻ ታማኝ ምንጮች ገልጸዋል።
    “እኔ መታሰሩና፤ በእስር ቤት እየደረሰብኝ ያለው ስቃይ አልከበደኝም። የከበደኝ ግን በኔ መታሰር ልትጠቀሙበት አለመቻላችሁ ነው። በኔ መታሰር መንግስት ብዙ ጫና ውስጥ እንዳለ ይታወቃል። በኔ መታሰር ብዙ ሥራ ልትሰሩበት፤ ትግሉን ወደፊት ልታስኬዱበት ስትሉ ይህን አላደረጋችሁም” ያለው አንዷለም አራጌ አሁንም የመንፈስ ጥንካሬው አብሮት እንዳለ በ እስር ቤት ካነጋገሩት ወገኖች መካከል ስማቸው እንዳይጠቀስ የፈለጉ የተቃዋሚ ፓርቲ አመራር ለዘ-ሐበሻ ገልጸዋል።
    አንዷለም አራጌ የፌደራሉ ማረሚያ ቤት የሚጠይቁህን ሰዎች ስም ዝርዝር አስመዝግብ ተብሎ ተጠይቆ የነበረ ሲሆን እርሱ ግን ማንም ሰው መጥቶ ሊጠይቀኝ መብቱ ነውና ስም ዝርዝር አውጥቼ አልሰጥም ሲል ፈቃደኛ አለመሆኑን ዘ-ሐበሻ ከዚህ ቀደም መዘገቧ አይዘነጋም።
    zehabesha
    posted by Aseged Tamene

    Friday, December 6, 2013

    የችግሮቻችን የመፍትሔ ቁልፍ – ወያኔን አስወግዶ ፍትህን ማስፈን


    አሁንም በሳውዲ አረቢያ እና አካባቢው አገሮች የሚገኙ ወገኖቻችን የድረሱን ጥሪዎች እያሰሙ ነው። የወገኖቻችን ዋይታና ሰቆቃ አልበረደም። ዛሬም እህቶቻን እየተደፈሩ፣ እየተዋረዱ፣ እየተገደሉ ናቸው። በጥጋብ አገር ውስጥ ሆነው ኢትዮጵያዊያን ሕፃናት በረሀብና በጥም እየሞቱ ነው። በርካታ ኢትዮጵያዊያን ለከፋ የአዕምሮ ህመም እየተዳረጉ ነው።
    በተለያዩ የዓለም አገራት የሚገኙ ኢትዮጵያዊያን በመካከለኛው ምሥራቅ የሚገኙ ወገኖቻቸውን ሕመም እየታመሙ፤ ስቃያቸውን እየተሰቃዩ ይገኛሉ። አስቸኳይ እርዳታ ለማድረስም አቅማቸው የቻለውን ሁሉ ለማድረግ በመረባረብ ላይ ናቸው።
    ባለፉት ጥቂት ሣምንታት ኢትዮጵያዊያን ባደረጓቸው ብርቱ ጥረቶች ጥቂት አበረታች ውጤቶች ተገኝተዋል። ከደረሰባቸው የመብት ረገጣ ጋር ፈጽሞ ተመጣጣኝ ባይሆንም ቢቢሲን ጨምሮ አንዳንድ የዓለም ዓቀፍ የዜና አውታሮች በወገኖቻችን ላይ ስለሚደርሰው በደል እንዲዘግቡ ማድረግ ተችሏል። እስካሁን ምን ያህል ወገኖቻችን እድሉን እንዳገኙ ማረጋገጥ ባይቻልም የሳውዲ መንግሥት ሙሉ የትራንስፓርት ወጪ ችሎ ወገኖቻችን ማጓጓዝ ጀምሯል። ዓለም ዓቀፍ የሰብዓዊ መብት ጥበቃ ድርጅቶች ለኢትዮጵያዊያን መብት መከራከር ጀምረዋል።
    በአንፃሩ ግን አሁንም ሕሊናን የሚረብሹ ነገሮች እየተሰሙ ነው።
    1. ከሳውዲ እየታፈሱ የመን ድንበር ላይ የተጣሉ፤ የደረሱበት የማይታወቁ ኢትዮጵያን ቁጥር በየእለቱ እየጨመረ ነው። እነዚህ ወገኖቻችን በየመን በረሀ ላይ የሚደርስባቸው ሰቆቃ ሳውዲ ውስጥ ከነበረው የባሰ ነው።
    2. አሁንም በሳውዲ ተደብቀው የሚገኙ፤ “እጃቸውን ለመንግሥት ሰጥተው” እንደ ወንጀለኛ በእስር ቤቶች የሚማቅቁ በአስር ሺዎች የሚቆጠሩ ኢትዮጵያዊያን አሉ። እነዚህ ወገኖቻችን ያሉበት ሁኔታ ሕሊና ሊሸከመው ከሚችል በላይ ነው።
    ከዚህ ሁሉ በላይ ኢትዮጵያዊያንን እየረበሸ ያለው የወያኔ ባህርይ ነው።
    ወያኔ በእንዲህ ዓይነት የመከራ ወቅትም በወገኖቻችን ላይ ዘርፈ ብዙ ንግድ እያጧጧፈ ነው። በሳውዲ አረቢያ መንግሥት ወጪ የተመለሰሉትን ወገኖቻችን ለምርጫ ቅሰቀሳ ፕሮፖጋንዳ ሥራ እየተጠቀሙባቸው መሆኑ ሳያንስ ለእለት ጉርስ የሚሰጣቸው የእርዳታ ገንዘብ በወያኔ እየተዘረፉ ነው። ገንዘብ ባለበት ሁሉ ወያኔ አለ። ወያኔ ለተመላሽ ስደተኞች የእለት ጉርስ የተሰጠውንም እርዳታ እየቀማ የሚበላ እኩይ ኃይል ነው።
    ድሆች ኢትዮጵያዊያን ወደ አረብ አገራት ሲሰደዱ ለወያኔ ድርጅቶች ገንዘብ ከፍለው ነው። እዚያ በነበሩበት ጊዜም ለወያኔ ገንዘብ እንዲከፍሉ ይደረግ ነበር። በግፍ ተፈናቅለው፤ ሀብታቸው ተዘርፎ ባዶ እጃቸውን ሲመለሱም ለወያኔ የእርዳታ ገንዘብ መለመኛ ሆነዋል። ወያኔ በድሆች ኢትዮጵያዊያን ድህነት የሚከብር በታሪካችን ውስጥ ታይቶ የማይታወቅ ስግብግብ ነው። ወያኔ ኢትዮጵያዊያን ፈጽሞ ሊጠየፉት የሚገባ ነው ስብስብ ነው።
    ግንቦት 7: የፍትህ፣ የነፃነትና የዲሞክራሲ ንቅናቄ በችግር ላይ የሚገኙ ወገኖቻችንን ከመርዳት ጎን ዓይኖቻችንን ከወያኔ እንዳንነቅል በአጽንዖት ያሳስባል። ወያኔ ከሥልጣን ሳይወገድ ችግሮቻችንን መፍታት አንችልም። የኢትዮጵያዊያን ችግሮች ለወያኔ የገቢ ምንጮች ናቸና ወያኔ እስካለ ድረስ ችግሮችን መፍጠሩና ማስፋፋቱ አይቀርም።
    የኛ የኢትዮጵያዊያን ችግሮች የመፍትሔ ቁልፍ ያለው ወያኔን በማስወገድ ፍትሀዊ አመራር ማስፈን ላይ በመሆኑ የጋራ ትኩረታችን እዚያ ላይ እንዲሆን ግንቦት 7 ያሳስባል።
     ድል ለኢትዮጵያ ሕዝብ!!!

    የኢትዩጵያ ህዝብ መቼም የማይዘነጋው እውነታ


    1463747_246984642126497_885575045_n
    ምንም ዛሬ ህወሃቶች በቅጥፈት ፕሮፓጋንዳ ሊያረሳሱት ቡሞክሩም እነሱ በ1998 ከሻብያ ጋር በዝርፊያ ክፍፍል ከመጣላታቸው እና በሰበብ ባስባቡ ጦርነት ከመዳደረሳቸው በፊት የሚያውቃቸው የኢትዩጵያ ህዝብ መቼም የማይዘነጋው እውነታ አለ። መለስ ዜናዊ የኢትዩጵያን ”ባንዲራ ጨርቅ ነው“ ብሎ ካንቋሸሸባት ግዜ ጀምሮ በየቢሮዋቸው፣ ሰርጋቸው እና በግል ቤታቸው ብቻ ሳይሆን በየአመታዊ በዓሉም ሆነ ሌላ የማህበራዊ በአል ላይ ህወሃቶች የእራሳቸውን ባንዲራ እንጂ የኢትዩጵያን ባንዲራ ሲያውለበልቡ አይታዩም ነበረ። እንደውም አረንጓዴ ቢጫ ቀይ ያገሩን ሰንደቅ አላማ ያውለበለበ ኢትዩጵያዊን ሰበብ እየፈለጉ ማጉላላት ልማዳቸው ነበረ።
    የኢትዩጵያ አምላክ የሻብያን እና የህወሃትን የጥላቻ ትዳር ከናደው እና እሳት እና ጭድ ካደረጋቸው በኋላ ብቸኝነት የተሰማው ህወሃት፣ ያለ ሌላው ኢትዩጵያዊ ድጋፍ ብቻውን ሻብያን መቋቋም እንደማይችል ያመነው ህወሃት፡ ባንዲራዋን ተሸክሞ የኢትዩጵያን ህዝብ ”ድረስልኝ፡በዚች ባንዲራ ከሻብያ አስጥለኝ!“ ብሎ ሲቀላምድ ያየው የኢትዩጵያ ህዝብ በልቡ ስቋል። ዛሬም እንደ ትላንትናው ነገሮች ሲከሩ እና ኢትዩጵያዊ በሙሉ በቡድንም በነጠላም ”ጠላቴ ህወሃት ነው!“ ብሎ ሲነሳበት እፍረተ ቢሱ ህወሃት ያችን ትላንት የጠላትን እና የናቃትን በንዲራ ተሸክሞ ሲማጸን ይታያል።
    ለእኔ በዚህች ሰዓት የኢትዩጵያን ባንዲራ የተሸከመ የህወሃት ደጋፊ፣አባልን እና ባለስልጣን እንደማየት የሚያረካኝ ነገር የለም። የልባቸውን ስሜት ብናውቅም ህወሃቶች እና መሪወቻቸው የኢትዩጵያን ባንዲራ ይዘው ስመለከት የሚገባኝ መልእክት ቀላል ነው — “ኢትዩጵያዊነት ሳንወድ በግድ አንበርክኮናል፣ መድረሻ እና መሸሸጊያ ስላጠን በጭንቀታችን ሰዓት ከኢትዩጵያዊነት ሌላ የሚያድነን እንደሌለ ተረድተናል፣ ይሄ የሰደብነው ባንዲራ እና የናቅነው ታሪኩ ትንሽ እና ተልካሻ የሆነውን እኛነታችንን ተመልክቶ ይማረን” የሚል የሽንፈት ጣር ነው !
    Samsson Dechassa
    source: freedom4ethiopian
    posted by Aseged Tamene

    Monday, December 2, 2013

    ሰልፍ ብቻ በቂ ነው ወይ? አንድ መላ እንበል….ተርበዋል፣ ተጠምተዋል..እንድረስላቸው በግሩም ተ/ሀይማኖት

    saudi-2-225x300
    በሳዑዲ ለተከሰተው ሁኔታ..ለወገን ድምጽ ለማሰማት ይህ ሁሉ ኢትዮጵያዊ በየሀገሩ የሚያደርገውን ሰላማዊ ሰልፍ ሳይ ልቤ ቅቤ ጥጥት ያደርግና ሳይበቃው አንድ ሀሳብ ውስጤ ስውጥ ብሎ ይጦልማል፡፡ እንደገና ብልጭ ይልና ምላሽ ፍለጋ ያንከራትተኛል፡፡ ‹‹..እያደረግን ያለነው በቂ ነው ወይ? ድብደባውም ይቁም የሞቱትም ይታወሱ…በህይወት ያሉትስ ምን ሁኔታ ላይ ነው ያሉት? በተለያየ ቦታ ታጉረው ምግብ እጦት፣ ውሀ ጥም..ሌላም ሌላም ችግር አለባቸው፡፡ ሀገር ሲገቡም ማረፊያ ቦታ የሌላቸው ሞልተዋል…ይህን ሳስብ ምን ብናደርግ ይሻለናል?›› የሚለው ጥያቄ በጉልህ ውስጤ ተጽፎ ምላሽ ይናፍቃል፡፡ አምጬ አምጬ..ውስጤ ሲላወስ ቆይቶ መፍትሄ ፍለጋ ከማውቃቸው ጋር ሁሉ ስወያይ ቆይቼ አንድ ስለሺ የተባለ ወዳጄ ከወደ ሀገረ እንግሊዝ ሀሎ ብሎ አማካረኝ፡፡ ውስጤ ያሰበውን ስለነገረኝ ወይም ምን ማድርግ እንዳለብኝ እያሰብኩ የነበረውን አወጋሁት፡፡
    የምናደርገው እንቅስቃሴ ብቻ በቂ አይደለም፡፡ በእርግጥ በታሪካችን ውስጥ ታይቶ የማይታወቅ ህብረት አሳይተናል፡፡ ለነገሩ ኢትዮጵያዊያን ስንነካ እንደ ንብ ግር ብለን ህብረታችንን እናሳያለን፡፡ ግን ይህ ብቻ በቂ ነው ወይ? የገቢ ማሰባሰቢያ ማድረግ እና በማጎሪያ ቦታ ያሉትን ምግብ የምናቃምስበት ሁኔታ ቢፈጠር ጥሩ ነው፡፡ ሀገር የገቡትስ ቢሆን ነገ ጎዳና አናያቸውም ብሎ ማሰብ ሞኝነት ይመስለኛል፡፡ ከሳዑዲ ከመጡት ውስጥ የተወሰኑትን ለማናገር ሞክሬ ነበር፡፡ 12 እና 13 አመት ሳዑዲ ሲኖር እናት አባቱ ሞተው ቤቱን ቀበሌ የተረከበበት ሁኔታ ያጋጠመው ልጅ እንዳለ..መግቢያ የሌለው በፊትም ቤተሰብ አጥቶ በባህር የወጣ አለ፡፡ ዛሬ የት ነው የሚገባው አግብቶ ወልዶ ያለም አለ ዛሬ የት ነው የሚመለሰው ቤተሰብ ላይ…ሁሉም ምላሽ የሌላቸው አሳሳቢ ነገሮች ናቸው፡፡
    ገቢ አሰባስበን አንድ ነገር ማደድረግ እንዳለብን ይሰማኛል፡፡ እናንተ ምን ትላላችሁ? በውጭ ያሉ አርቲስቶችም ቢሆን የገቢ ማሰባሰብ ዝግጅት ቢያደርጉ በጣም በደስታ ብዙዎች እንደሚሳተፉ አምናለህ ወገን ለወገኑ የቻለውን ለማድረግ ወደ ኋላ አይልም የሚያሰባስበው ማጣት ይመስለኛል፡፡ እባካችሁ አንድ መላ እንበል….ተርበዋል፣ ተጠምተዋል..እንድረስላቸው

    ሃገሪቷን የስደት ሃገር ያደረገው ራሱ መንግስት ነው


    Posted: November 30, 2013 in Uncategorized
    0
    • “ዜጐች የተሰደዱት መንግስት የሥራ ዕድል ባለመፍጠሩ ነው”
    መንግስት ከሣውዲ የሚመለሱ ዜጐች ቁጥር አስቀድሞ ከተገመተው በላይ መሆኑን ገልጿል። ቀድሞ የተመላሾቹ ቁጥር  “ዜጐች የተሰደዱት መንግስት የሥራ ዕድል ባለመፍጠሩ ነው”
    28 ሺህ እንደሚሆን ቢገመትም አሁን ወደ 80ሺህ እንደሚደርስ ተነግሯል፡፡ በስደተኞቹ ላይ እየደረሰ ያለውን እንግልት 
    የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ ዶ/ር ቴዎድሮስ አድሃኖም፤ ባገኙት አጋጣሚ ሁሉ ከማውገዝ አልተቆጠቡም፡፡ ጉዳዩ በሰከነና 
    የዲፕሎማሲ መርሁ በሚፈቅደው መንገድ መያዙንም ገልፀዋል፡፡ መንግስት ከዚህ በላይ በዲፕሎማሲው ርቆ ሊሄድባቸው 
    የሚችልበት አማራጮች  እንደሌሉ የሠሞኑ መግለጫዎቹ ያመለክታሉ፡፡ ይሁን እንጂ የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ የፖለቲካ 
    ሣይንስ ምሁሩ ዶ/ር መረራ ጉዲና፣ መንግስት የዜጐቹን መብት በማስከበርም ሆነ የሃገርን ክብር በማስጠበቅ ረገድ ምንም 
    አልተራመደም ይላሉ – ተመላሾቹን ከመቀበል የዘለለ ዲፕሎማሲያዊ እርምጃዎች መውሰድ አለመቻሉን በመግለፅ፡፡ ዶ/ር 
    መረራ ጉዲና በጉዳዩ ዙሪያ የሰጡንን አጭር ማብራሪያ እነሆ:-
    በሣውዲ አረቢያ በዜጐቻችን ላይ እየደረሰ ያለውን በደል ተከትሎ መንግስት ጉዳዩን የያዘበትን መንገድ እንዴት 
    ገመገሙት?
    ሁለት ሶስት ነገሮች አሉ፡፡ አንደኛው አሜሪካ፣ ጀርመን፣ ስዊድን በመሳሰሉት ሃገሮች ያሉ ኢትዮጵያውያን በሣውዲ 
    አረቢያ ላይ ተቃውሞ ሲያሰሙ እየፈቀዱላቸው፣ እዚህ መከልከሉ በዜጐች ላይ ተጨማሪ ወንጀል መስራት ነው፡፡ 
    ሁለተኛው በተለያየ መንገድ እየሰማን እንዳለው አሁንም ቢሆን በ40ሺህ የሚቆጠሩ ዜጐች እየተንገላቱ ነው፡፡ እሪታና 
    የይድረሱልን ጥሪ እያሰሙ ነው። የኢትዮጵያ መንግስት ደግሞ የሚያወራው ሌላ ነው፡፡ መደብኩ እንኳን ያለው 50 
    ሚሊየን ብር አንድ እነሱ “የመንግስት ሌባ” የሚሉት የሚሠርቀው እኮ ነው። 50 ሚሊየን ብር ለ70ሺህ ሰው ነው 
    የመደቡት። ነገር ግን በሙስና የተከሰሱት ሰዎቻቸው እኮ የዚያን ሶስት እጥፍ ሰርቀዋል ተብሏል፡፡ በእውነቱ የተመደበው 
    ገንዘብ በጣም ትንሽ ነው፡፡ ሌላው ደጋግመው የሚያሰሙት፤ የሣውዲ አረቢያ መንግስትን ድርጊት የሚኮንን ሳይሆን 
    ወዳጅነት እንዳይበላሽ ትልቅ ስጋት ያላቸው የሚያስመስላቸው ነው፡፡ ከዜጐች ድብደባ፣ ግድያና እንግልት ይልቅ 
    የሣውዲ መንግስት ፍቅር የያዛቸው ነው የሚመስለው፡፡ ስለዚህ በሚፈለገው መንገድ ለጉዳዩ ምላሽ እየሰጡ አይደለም 
    የሚል መደምደሚያ ላይ መድረስ ይቻላል፡፡ ድሮውንም ቢሆን እነዚህ ዜጐች የተሰደዱት የኢትዮጵያ መንግስት የስራ 
    እድል መፍጠር ባለመቻሉ ነው፡፡ ሃገሪቷን የስደት ሃገር ያደረገው ራሱ መንግስት ነው፡፡
    በሃላፊነትም ያስጠይቀዋል፡፡ ስለዚህ መንግስት በቀን ይሄን ያህል ሰው መለስኩ ከሚል፣ በመሠረታዊነት ዜጐች 
    የማይሰደዱባት ሃገር መፍጠር አለበት፡፡ የስራ እድል ሊኖርና የሰብአዊ መብት ሊከበር ይገባል፡፡
    መንግስት በዜጐቹ ላይ ለተፈፀመው ግፍ፣ በአለማቀፍ ፖለቲካዊ ዲፕሎማሲው ምን ድረስ ነው ሊሟገት የሚችለው?
    መንግስት እኮ ደጋግሞ የሚነግረን በህገወጥ መንገድ ከሃገር የወጡ ናቸው እያለ ነው፡፡ እንኳን በዚህ ዘመን ቀርቶ በጥንት 
    ዘመንም ስደተኞች ክብር አላቸው፡፡ ዝም ብሎ ይገደሉ፣ ይፈለጡ፣ ይቆረጡ አይባልም፡፡ ስለዚህ ሣውዲ አረቢያ ኋላቀር 
    በሆነ መንገድ ዜጐቻችንን ስታንገላታ በህግ መክሰስም ይቻላል፡፡ ሌላ አማራጭ ከተፈለገም እንደወዳጅ መንግስትና 
    የንግድ ሸሪክ ብዙ ተጽእኖ ማድረግ ይቻላል፡፡ ይልቁንስ የኢትዮጵያ መንግስት እያየ ያለው፣ እዚህ ያሉ ተቃዋሚዎች ምን 
    አሉ የሚለውን ብቻ ነው፡፡ ተቃዋሚዎች ከሰሱን፣ አጣጣሉን የሚለው ላይ ነው ያተኮረው፡፡
    ከዚያም ሲያልፍ ሌት ተቀን እንደ መጽሐፍ ቅዱስ የሚነግረን ዜጐቹ በህገወጥ መንገድ መሄዳቸውን ነው፡፡ ዋናው ጉዳይ 
    መጀመሪያ የዜጐችን ነፍስ ማዳን ነው፤ ሌላው ደግሞ ለስደት የዳረገንን የኢኮኖሚ ችግር በመፍታት፣ ኢትዮጵያን ከስደት 
    ሀገርነት ዝርዝር ለማውጣት መንቀሳቀስ አለበት፡፡ ግን አሁን ባለው ሁኔታ የዚህ አዝማሚያ እምብዛም እየታየ አይደለም፡፡
    መንግስት በሣውዲ አረቢያ ላይ ይከተል የነበረውን የዲፕሎማሲ አቅጣጫ ለመፈተሽና ለመቀየር የእነዚህ ዜጐች እንግልት 
    ምክንያት ሊሆን ይችላል ብለው ያስባሉ?
    አሁን እኮ መንግስት ጠንከር ያለ መግለጫ እንኳ አላወጣም፡፡ በመኮነን ደረጃ እንኳ ደፍሮ መግለጫ ማውጣት 
    አልቻለም፡፡ ሌሎች ሀገሮች እኮ ቢያንስ በዜጐቻቸው ላይ በደል ሲፈፀም በመንግስት ደረጃ የመረረ ጩኸት ያሰማሉ፡፡ 
    የኢትዮጵያ መንግስት ግን ከህዝቡ ጋር አብሮ ሊጮህ ቀርቶ፣ የህዝቡንም ድምጽ እያፈነ ነው፡፡ ለዚህ ነው በተለይ 
    በፖለቲካ ዲፕሎማሲው በኩል እየተወሰደ ያለው እርምጃ በቂ አይደለም የምለው፡፡
    መንግስት ዜጐቹን ከሃገሪቱ ከማስወጣት ባለፈ እርምጃ ያልወሰደው የኢኮኖሚ ጥገኝነት ጉዳይ ስላለ ነው፤ የኢትዮጵያ 
    ዋነኛዋ የውጪ ንግድ ሸሪክ ሣውዲ በመሆኗ ነው የሚሉ አስተያየቶችንስ እንዴት ያዩዋቸዋል?
    በእርግጥ የኢኮኖሚ ጥገኝነቱ አለ፡፡ እናውቃለን። ታላላቅ የሣውዲ አረቢያ ከበርቴዎች በዚህች አገር ኢንቨስት ያደርጋሉ፡፡ 
    ነገር ግን ለኢኮኖሚ ሲባል የዜጐችን መብትና ብሔራዊ ጥቅምን አሣልፎ መስጠት በየትኛውም የፖለቲካ አማራጭ ፈጽሞ 
    አይመከርም፡፡ ከምንም በላይ የዜጐች መብትና የሃገር ክብር ይቀድማል፡፡ በመቶ ሺህ የሚቆጠር ሰው እየተንገላታ 
    ለኢኮኖሚ ጥገኝነቱ ሲባል ዝምታን መምረጥ እንዲሁም የዜጐችን ጩኸት ወደማፈኑ መሄድ ተገቢ አይደለም፡፡
    አንድ መንግስት በሌላ ሀገር የሚኖሩ ዜጐቹን መብት ለማስከበር ከአለማቀፍ ህግና ፖለቲካ ተመክሮ አንፃር ምን ያህል 
    ርቀት ነው ሊጓዝ የሚችለው?
    ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነትን ጨርሶ እስከማቋረጥ ይደርሳል፡፡ ከዲፕሎማሲ ግንኙነት ማቋረጥ ባለፈም ችግሩን ለአለማቀፉ 
    ህብረተሰብ በጩኸት ማሰማትም ይገባል፡፡ የኢትዮጵያ መንግስት ግን አፉን ሞልቶ ‘በዜጐቻችን ላይ እየተሰራ ያለውን 
    ግፍ እንኮንናለን’ ለማለት እንኳ እየጨነቀው ነው፡፡ እዚህ ያለውን ኤምባሲ እንኳ ሲያነጋግሩ፣ ዋናውን አምባሳደር 
    አይደለም፡፡ በሰለጠኑትን ሃገሮች ደረጃ ቢሆን በ30ሺህ፣ 60ሺህ የሚቆጠሩ ዜጐች እንዲህ ያለ እንግልት ሲደርስባቸው 
    ቀላል ጉዳይ አድርገው አይመለከቱትም፡፡ የህንድ፣ የፊሊፒንስ እና የሌሎች ሃገሮች ዜጐች ከኢትዮጵያውያኑ በተለየ 
    ክብራቸው ተጠብቆ ነው ከሃገር የወጡት፡፡ ይሄ ለምን ሆነ ብሎ መጠየቅ ያስፈልጋል፡፡
    የስደተኞቹ ስቃይ ለፖለቲካ መጠቀሚያነት እንዳይውል መንግስት ጠይቋል፡፡ በእርግጥ ለፖለቲካ መጠቀሚያነት ውሏል?
    የኢትዮጵያ ዜጐች በያሉበት ብሶት እያሰሙ ነው። በተለያዩ መንገዶች በየሃገራቱ በኢትዮጵያውያኑ ላይ የሚፈፀሙት 
    በደሎች ሲሰሙ ይዘገንናሉ፡፡ እኛ እኮ እየጠየቅን ያለነው የእነዚህ ኢትዮጵያውያንን መብት ነው፡፡ ነገር ግን መንግስት 
    ጉዳዩን በሌላ እየተረጐመው እኮ ነው የተቸገረው፡፡